ልጥፎች

ንጉሥ እስከ ሠራዊቱ የተሰለፈበት #ሚስጢራዊ ክስተት።

ምስል
  ንጉሥ እስከ ሠራዊቱ የተሰለፈበት #ሚስጢራዊ ክስተት።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰።       #እፍታ ።    እንዴት አመሻችሁ ማህበረ ቅንነት። የተፎካካሪ፤ የተደማሪ የፖለቲካ ድርጅቶች የፋና መድረክ የምዕራፍ ፩ የማጠቃለያ ቁጭት ፎቶ ይህን ይመስል ነበር። ስክሪን ላይ ያነሳሁት ነው።   ይህ ቃለ ምልልስ ከተካሄዴ በኋላ በርካታ ኢትዮጵውያን የግል አስተያዬታቸውን በአጭርም፤ በረጅምም፤ በቁጣም፤ በተግሳጽም፤ በክብርብርም - በኩሰትም፤ በቁጭትም - በተስፋ ምልዓትም የኢትዮጵያ የፖለቲካ መንፈስ ጥሩ አድርርጎ አገላብጥ ሲገመግመው ሰነባብቷል። በመጀመሪያ ላይ ይህን ያህል ይሆናል ተብሎ አልነበረም።    የሆነ ሆኖ የብልጽግና ሁነኛ የሚባሉ አክቲቢስቶች፤ ሚዲያወችም ያልጠበቅኩት #አወንታዊ ዕይታ የሰጡትን አዳምጫለሁኝ፤ ጹሁፋንም አንብቤያለሁኝ። ብልፄው ለምን ተደፈረ ያሉም ፊት ለፊት ወጥተው ሲሞግቱ አይቻለሁኝ። ጥሩ ነው። አስደሳችም ነው።    ወጣቶች በራሳቸው የዘመን ፖለቲካ በዚህን ያህል ፍጥነት ግሎባል ንቅናቄ መፍጠር ለቀጣዩ የምርጫ ጊዜ ምርጫው እኔንም ይመለከተኛል የሚል ጤናማ ዕድምታ ይፈጥራል። አክሰሱ ያላቸው ታዳጊ ወጣቶችም ነገም እኔ እንዲህ ብሆን የሚል ስሜት ሊያድርባቸው ይችላል።    ስለሆነም እኔ ከጠበቅኩት በላይ የተሳትፎ ህብራዊነት በትጋት እና በተከታታይነት ስለየሁ አወንታዊ ስሜት ውስጤ ተመግቧል። በብልጽግና የፖለቲካ ፓርቲ መሪ አካላት እኔን የተሰማኝ ያህል ሊሰማቸው ላይችል ይሆናል። አገር ነገ ለሚሉ ኢትዮጵያዊ ዜጎች ግን የወጣቶቻችን ሙሉ ተሳትፎ አበረታች ነው።   በሌላ በኩል የለት ዕ...

Par two, ብርድብርድ ያለው የትናንት የፋና የ2018 የምርጫ መድረክ የቤተ - ዳዊት መወደሪያ ምሽት።

  ብርድብርድ ያለው የትናንት የፋና የ2018 የምርጫ መድረክ የቤተ - ዳዊት መወደሪያ ምሽት።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰።   #ጠብታ ።   ሴት የፖለቲካ ሊቃናት የፖለቲካ ውክልና አጡ ብዬ ስሞግት ኖሬ፤ ዕድሉ ሲገኝ እንዲህ እና እንዲያ ማለት ስለሚፈትነኝ እንዲህ ካልበዛ በስተቀር እንዳላየሁ አይቼ የማልፋቸው ብዙ ጉዳዮች አሉ። የሆነ ሆኖ ያን ግዙፍ ተቋም የሚመሩ የፍትህ ሚር ትናት በነበራቸው የብልጽግና ፓርቲ ወካይ የሙግት ቆይታ የብልጽግና አቅም እጅግ #ፈተና ውስጥ ገብቶ ነበር ማለት ይቻላል። እንደ አለፈው ጊዜ በዕለቱ የማያፈናፍኑ ንቁ እና ትጉህ ሞጋቾች ቢኖሩ ምን ይበጃቸው እንደነበር አላውቅም።   ባለፈው ጊዜም ቢሆን ለጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ በጣም የቅርብ ሚር የሆኑት፤ በወሳኝ የጠቅላይ ሚሩ ልዑካዊ ጉዟቸው የማይለዩ፤ ለግሎባል መሰናዶ ተመራጭ የሆኑት፤ በዘመነ አብይዝም የመጀመሪያው የካቢኔ አወቃቀር ላይ የነበሩት ቁጥር ፩፤ በሲነሪቲ ደረጃ መቅድም የሆኑት ዶር ፍጹም አሰፋም እንኳን ከፋክት፤ ከጭብጥ ይልቅ #ፕርፖጋንዳዊ ሁነቶች ላይ ነበር ያተኮሩት። ይህም ቢሆን ይሻላል ከትናንቱ ብርድ ብርድ ከአለው የፋና የትናንት መድረክ።   እርግጥ ነው በዚህ የሙግት መድረክ ዕቅዳችሁ ምንድን ነው። የዕቅዳችሁ ፖሊሲ በምን ላይ ያተኩራል፤ ለአፈፃጸሙ ምን ያህል መሰናዶ አላችሁ? በፋይናንስ፤ በሰው ኃይል፤ በመንፈስ፤ በኮኦርድኔሽን ወዘተ ጥያቄው ይህ ነው። ቲም ሚር ዶር ፍጹም አሰፋ ግን ባለፋት የመምስት ዓመታት ክንውን ዘገባ አቅራቢ ነበር የሆኑት።   ለነገሩ የብልጽግና ፓርቲ ሁለቱ ምክትል ፕሬዚዳንቶችም ማኒፌስቶ ለቀጣይ፤ ትልም ለቀጣይ፤ ራዕይ ለቀጣይ ሲጠየቁ ማኒፌ...