ልጥፎች

"የኢትዮጵያ ፖለቲካ እና የአፍሪካ ቀንድ ሁኔታ"፣ ውይይት ከፕሮፌሰር ብሩክ ሃይሉ ጋር

ምስል

ነፃነት በራስ የመተማመን አቅም ነው፥ ምንጭም ነው። Eigenständigkeit. Freiheit. Selbstvertr...

ምስል

"ህዝቡ ሁለቱንም አይፈልግም!" አምባሳደሩ ህወሓት መሳሪያ የቀበረበትን ቦታ አጋለጡ!

ምስል

ፋይዳ ቢስ የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት፣ የፋኖ ድል ዜናዎች፣ የተሰነጠቀው የህወሓት ቤት #amhara #fano #tplf #...

ምስል

ኢትዮጵያ ህግ ናት። ይህን ማንነቷን ማስቀጠል የሁለችንም መብታዊ ግዴታችን ነው። Kinder; Die Alten, di...

ምስል

መርህ መኖርን ሥልጡን ያደርጋል። Prinzip. Gesetz. Regel. Dogma. Verfassung. Moralisc...

ምስል

ኮከቧ ኢትዮጵያዊ የR & B ዘፋኝ - የግራሚ አባል ናት፣ ከኩል ኤንድ ዘ ጋንግ እስከ ሀሊዉድ ተዋናይ ጋር መስራት...

ምስል

ፋኖ ባክግራውንዱ "ሽፍትነት" አይደለም። ፋኖ አፈጣጠሩ ሲፈረካከስ ውሎ የሚያድረው የውራጅ ፖለቲካ ርዕዮት አልፈጠረውም።

  ፋኖ ባክግራውንዱ "ሽፍትነት" አይደለም። ፋኖ አፈጣጠሩ ሲፈረካከስ ውሎ የሚያድረው የውራጅ ፖለቲካ ርዕዮት አልፈጠረውም።   ሰማዕቱ የተከበሩ ጄኒራል ሰኃረ መንፈሳቸው ምን ይታዘብ ይሆን????    በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት፤ አሠራር፤ አቅም፤ አመራር እጅግ ጠንቃቃ እና ቁጥብ ነኝ። ዛሬ በዚህ ዕርስ ዙሪያ ስጽፍ የዜግነት #ተጋርቶዬ እራሱ እያሰቃዬኝ ነው። በአንድ ላይ ኢትዮጵያዊ መባል ምን ያህል ፈተና መሆኑን ያዬሁበት አጋጣሚ ነበር።    "አቤቱ ለአንደበቴ ጠባቂ አኑርለት።"   የማከብራችሁ የአገሬ ልጆች ዘለግ ያለ ሙግት ነው።   የማህበረ ኦነግ ፖለቲካ - ልቅነቱ ብቻ አይደለም የሚያስገርመኝ። ይልቁንም የቁንጮ መሪወቹ የህግ ጥሰት #ህጋዊነት እንጂ። ብልሽቱን እኮ አስተካክሎ ማቅረብ ለካስ ይህም መሰጠትን ይጠይቃል። ሳይመረኝም፤ ሳያንገፈግፈኝም የኢትዮጵያ ኢታማጆር ሹሙ ጄኒራል ብርኃኑ ጁላ ከሉዓላዊ ሚዲያ ጋር የነበራቸውን ቆይታ ሁለቱንም አዳመጥኩት። መጥኔ ለአንቺ ኢትዮጵያ አልኩኝ።    እነ ክቡር ጄኒራል ፈንታ በላይ እና ፍፁም ድንቅ እና ብቁ ጓዶቻቸው የነበሩባት አገር እንዲህ እና እንዲያ ስትንገላታ፦ ወጀብ ሲንጣት ማዘን የሚለው ቃል አይገልፀውም። አቅምስ አቅልስ የት ይሸመት??? ለምን ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ በዬጊዜው የሚበውዙት የካቢኒያቸው፤ እንዲሁም "የብልጽግናቸውም" #ኮሚሳርያት አድርገው ደርበው አይሾሟቸውም የኢትዮጵያን ኢታማጆር ሹሙን። የኢትዮጵያ አዬር መንገድን እና የኢትዮጵያ አዬር ኃይልን እንዳጣመሩት።    ሥርዓት ለኦነግ ፖለቲካ አጀንዳው አይደለምና። ወይንም ላም ጣም በሌላቸው የዶር ለገሰ ቱሉን #የኮሚኒኬሽን ቦታን አይሰጧቸው??? አንደበቴ፤ ልሳኔ ስለሆኑላቸው። ለነገሩ ጄኒራል ብ

የአማራ ህዝብ ከቶ ወደ #ማርስ ይምጠቅላችሁን?????? ሞፈር ቀንበርን ለምን #ታነዱታላችሁ??? የአማራን #ገበሬ ለምን #በድሮን ታነዱታላችሁ? መሬቷንስ ለምን #በቦንብ መርዝ ታነዟታላችሁ? "የቤትህ ቅናት በላኝ።"

  የአማራ ህዝብ ከቶ ወደ #ማርስ ይምጠቅላችሁን?????? ሞፈር ቀንበርን ለምን #ታነዱታላችሁ ??? የአማራን #ገበሬ ለምን #በድሮን ታነዱታላችሁ? መሬቷንስ ለምን #በቦንብ መርዝ ታነዟታላችሁ?    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   እህል አልባ መኖር አለን? ዘር አልባ የሰው ልጅ ይቀጥላልን? ውኃስ አልባ መተንፈስ ይቻል ይሆን?    የኦነግ ጠረን የተላበሰው የኦህዴድ ወራሽ ብልጽግና የአማራ መሬት ይመረዝ ዘንድ ተግቶ እዬሰራ ነው። ለትውልድ እንዳይደርስ አርቆ በማሰብ ጠፍ የማድረግ ብቻ ሳይሆን በተመረዘ መሬት የሚበቅል አዝዕርት ለትውልድ የአካል አፈጣጠር እክል ይሆናል። #ገበሬን በቦንም?    ገበሬን በአውሮፕላን #መጨፍጨፍ ? ምን ይባል።    በአማራ ህዝብ ተገድሎም፤ ተዘርፎም፤ ተገሎም፤ ታስሮም፤ ተሰውሮም፤፦በገፍ በዬተገኘበት ተጨፍጭፎም የተረፈው በራህብ ያልቅ ዘንድ የጠቅላይ ሚር አብይ መንግሥት ተግቶ እዬሠራበት ይገኛል። የምርት ሰዓት፤ የእርሻ ወቅት ጠብቆ ይቀጣል ያሳዳል። ሲያሻውም ሰብሉን መስክ ላይ የዶግ አመድ ያስደርጋል። የአገር ልጅነቱን ፍቆ የውጭ ወራሪ ነው የሚመስለው። መሃከነ።    የሚገርመኝ አብረው የሚሠሩት የአማራ ግዑዛን ናቸው። ህሊና የሚባል ያልሠራላቸው #ገደላገደሎች ። እኔ የገበሬ አደራጅ ነበርኩኝ። በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን መሪ በአካል አግኝቼ ነበር። እናም መልሼ ላላገኝሽ እችላለሁ እና ምን ላድርግልሽ ሲሉ በትህትና ጠየቁኝ። ጎበዝ ተማሪ ነኝ። ውጭ አገር ለትምህርት ላኩኝ አላልኩም። ወይንም አዲስ አበባ የተሻለ ሥራ ይሰጠኝ አላልኩም። ወይንም እዚህ ሥራ ይሰጠኝ አላልኩም።   የጠዬቅኩት ገበሬ መንደር ሄጄ ገበሬ ማደራጀት ነው እምፈልገው አልኩኝ። እኔ የጎንደር ከተማ ልጅ ነኝ። ቤተሰቦቼም ባላባቶች ስለሆኑ ገጠሩን