ልጥፎች

#የይቅርታ #ደወል፤ የምህረት ዓዋጅ ለሁላችንም ያስፈልገናል። ሰሞናተ - አጽዋማት የክርስትና ይሁን የእስልምና ሃይማኖት በአጽህኖት ይህን ያጠይቃሉ እና።

ምስል
  #የይቅርታ #ደወል ፤ የምህረት ዓዋጅ ለሁላችንም ያስፈልገናል። ሰሞናተ - አጽዋማት የክርስትና ይሁን የእስልምና ሃይማኖት በአጽህኖት ይህን ያጠይቃሉ እና።    "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።" .           #ምዕራፍ ፲፰   ለሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሊቃናት #ከሊቅ እስከ #ደቂቅ በአክብሮት እምጠይቃቸው ውስጣችሁ #ለምህረት ፤ #ለይቅርባይነት #ቅርብ ይሆን ዘንድ ብትፈቅዱለት።   ዛሬን የተሰጠንን ቅዱስ ቀን #ካቴና ላይ ስለሚገኙ ወገኖቼ ሰጥቸዋለሁኝ። ስለሆነም ዛሬን አብረን እንሆን ዘንድ ዘንከት ባለ ኢትዮጵያዊ ትህትና #ቅኖቼን እጠይቃለሁኝ።   እኒህ አባት፤ ጋዜጠኛ፤ ጸሐፊ፤ ደፋር ሞጋች፤ ርትዑ፤ የታሪክ አዋቂ ከአቦይ ስብኃት፤ ከአቶ በረከት ስምኦን፤ አሁን ከጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ጋር በሚር ማዕረግ ፈርሰስ ከሚሉት ከአቶ ጌታቸው ረዳ፤ የጦር መሪ ከነበሩት ከጄኒራል ፃድቃን አይደለም በላይ፤ አቻ የሚሆን ግድፈት ፈጽመዋልን? ይህን ያህል አሳራቸውን የሚዩት?   ወይንስ አዘውንትነታቸው ተጠልቶ ይሆን? #እርግማንም ነው። አንድ መሪ ከቂም እና በቀል የጸዳ መንፈስ ሊኖረው ይገባል። #የምህረት እና የይቅርታም #ሞዴል ሊሆን ይገባል። በመሪነት ውስጥ አንዱ የቅርብ ዜጋ፤ ሌላው የእዳሪ ሊሆን ፈጽሞ አይገባም። መሪነት የውሃ ቅዳ፤ የውሃ መለስ #የኩታራ ድልቂያ አይደለምና።    በብዙ ነገር ዝልቅ ትዕግሥት የሚደረገው አቅም አግባቡን ስቶ ሌላ ላይ እንዳያርፍ ለጥንቃቄ ነው። እንጂማ ……… ያ ሁሉ የኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኛ የተፈታበት ሁነኛ ጎዳናን ዓመት ድገም የሚል ፈጣሪ ከመንበሩ ለቆ አይደ...

#አብይዝም እና ሥነ - መንግሥታዊ #ፕሮቶኮል።

ምስል
  #አብይዝም እና ሥነ - መንግሥታዊ #ፕሮቶኮል ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።"       #ምዕራፍ ፲፰።   ኢትዮጵያ ትልቅ አገር ናት ማለቱ ብቻ በቂ አይደለም።    ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ለፕሮቶኮል ሥርዓት የሚመቹ #መሪ አይመስሉኝም። በፕሮቶኮላዊ ዲስፕሊን ሥር ለመንቀሳቀስም የሚፈቅዱ አይመስለኝም። ይህን ለ፱ኛ ዓመት ዋዜማ ላይ ከሚገኘው የመንግሥታቸው አፈፃጸም ሂደት ግብረ መልስ ያገኜሁት መረጃ ነው።   ቀድሞ ነገር በአብይዝም #ፕሮቶኮል ሙያ እንደሆነ አብይዝም ይቀበለዋል ብዬ አላምንም። ለአፍሪካው ስብሰባ መሪወች አቀባበል ሲደረግላቸው አንዲት ሴት አይቻለሁኝ። ይህ በተቋም ደረጃ ይሁን አይሁን አላውቅም። ወይንም የአፍሪካው ህብረት አዘጋጅቶ ይሁን አላውቅም።   የሆነ ሆኖ አንድን አገር እንደ መንግሥት #ሊያቆመው ፤ #ሊያጸናው ፤ ሊያስከብረው ከሚችሉ በኽረ ጉዳዮች መካከል #ሥርዓት ወሳኝ ጉዳይ ይመስለኛል። በአብይዝም ዘመን የፕሮቶኮል ሹም የሚባልም ሰምቼ አላውቅም። በደርግ ጊዜ የኮነሬል መንግሥቱ የፕሮቶኮል አገልግሎት የሚሰጡ ደልደል ያሉ ፍጹም ታማኝ ሴት እንደነበሩ አስታውሳለሁ። ይህ በተዋረድ በክ/አገር፤ በአውራጃ እና በወረዳ በጽህፈት ቤት አገልግሎት ሥር ይመራ ነበር።    አቀማመጥ #በሲነሪቲ ነው። ዝንፍ የለም። አለባበስም በስብሰባ #ደማቅ ሰማያዊ ካኪ፤ በመደበኛ ሥራ ካኪ ቀለም እና ድብ ያለ ድባ ነገር ይለበሳል። እኔ አመጸኛ ነገር ነበርኩኝ። ቅዳሜ እና እሁድም፤ ዓውድ ዓመታትም ሥራ ላይ ስለነበርን በእነኝህ ቀናት ካኪ አለብስም ነበር። የተለዬ ልብስ ለብሼ ነበር ቢሮ እምገባው። ትርፍ ሰዓቴ ስለሆነ።   እራሱ ካኪውን በፋሽን ዲዛ...

የኢትዮጵያ Mastermind ለመሆን የተሰለፋ አገራት እና የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ መጥኖ የመነሳት መቅኖ አስፈላጊነት።

ምስል
  የኢትዮጵያ Mastermind ለመሆን የተሰለፋ አገራት እና የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ መጥኖ የመነሳት መቅኖ አስፈላጊነት።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰   ብዙ በጣም ብዙ ሁነቶች በኢትዮጵያ ሰሞኑን ተስተናግዷል። በላይ በላይ ፋታ አልቦሽ ሁነቶችን ሳይ በ2010 እኢአ ስደት ላይ የነበሩ ኢትዮጵውያን፤ የፖለቲካ ድርጅቶች፤ አገሮች ሁሉ ወደ ኢትዮጵያ ይጓዙ ነበር። ፖለቲካው ገና #ችግኙ ከፈልነት ሳያልፍ የገነገኑ ሁነቶችን እንደምን ማኔጅ ማድረግ እንደሚቻል እራሱን የቻለ አካልም ሳይኖር የነበረው ዲል ያለ ሁነት ይገርመኝ ነበር። ጎንደሮች ባለቅኔ ናቸው። ይህን መሰል ሁነት ሲገጥም "ራስ ሳይጠና ጉተና" ይሉታል።   ሰሞኑን ያዬሁትም አብይዝም የ፯ ዓመታት ልምድ ቢኖረውም፤ በጎኑ ማን አለ እራሱን የቻለ ተብሎ ሲታሰብ አንድ ሁለት ሊኖሩ ቢችሉም ብዙው የአብይዝም ቀጥተኛ መንፈስ ጥገኛ ነው። ከንቲባ ጽህፈት ቤትን፤ ጠቅላይ ሚር ቢሮን፤ ውጭ ጉዳይ ሚኒስተርን ለናሙና ማንሳት እችላለሁኝ።   አብዛኛው የሁለመና ሁነት የአብይዝም መንፈስ ጥገኛ ነው። ይህ ደግሞ አደጋው ብዙ ነው። እንጂ፤ እንጂማ በዚህ ወላፈን ውስጥ የማይቀርበትን አንዱን ኢቬንት ከውን፤ ለሌላው በቂ ጊዜ ሰጥቶ፤ አስታግሶ ፤ ሳይጠዳደፋ፤ ትንፋሽም ሰብስቦ ማስተናገድ ይገባ ነበር። -------------- የገረመኝ ደግሞ፤ በዛ ሁነት ሰንብተው ጠቅላይ ሚኒስተሩ ትናንት ወለጋ ነበሩ፤ በ100 ቀናት ውስጥ ዶር ለማ መገርሳን እና እሳቸው የተሞገቱበት ደንቢደሎም በጉብኝቱ ተካታ ተመልክቻለሁኝ። ያን ጊዜ ጽፌበትም ነበር ስለ ነገረ ደንቢደሎ፤ ሊዮዋቸው እንኳን ፈቃደኞች አልነበሩም። አኩርፈው ነበር የተቀበሏቸው።    ብቻ፤ አወን ብቻ...