ኢትዮጵያም የአማራ ህዝብም ሚስ ያደረጓቸው ጨዋ፤ ጭምት፤ አስተዋይ ሰብዕና። ብልፄው የደግነቱ ልክ ለፓርላማ የክብር አባልነት #በቻሪቲ። #በምደባ አገር ምድሩን አንበሸበሸ።
ኢትዮጵያም የአማራ ህዝብም ሚስ ያደረጓቸው ጨዋ፤ ጭምት፤ አስተዋይ ሰብዕና። ብልፄው የደግነቱ ልክ ለፓርላማ የክብር አባልነት #በቻሪቲ ። #በምደባ አገር ምድሩን አንበሸበሸ። #አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፱። ብልፄው ለውስጦቹ የፓርላማ ወንበር #ቻሪቲ በ7ኛው ምርጫ ገፋ አድርጎ አንበሽብሿቸዋል። መጠራቅቁ ከተቻለ። ወጥ ሃሳብ። ወጥ ፍላጎት። የሁሉ እሽታ እና ይሁንታ በገፍ ……… የማያጓጓ የማይስብ ይሆናል። በድርጅታዊ ሥራ ሞጋች ተሁኖ ሊወጣ ይችል ይሆናል። ያለፍጥረቱ ያለልኩ የተሰፋ እጀ ጠበባ ወይንም ጥብቆ ይሆናል። እራስን የሚያጸናው የራስ ጥረት ብቻ ነው። በሙሉ ጥገኝነት እና ጥገና እራስን ለማግኜትም፤ ሆነ ለመሆን ጋዳ ይሆናል። #ዕፍታ ። ለሰከነ፤ ምራቁን ለዋጠ፤ ጥድፊያን ሃራም ለሚል ሰብዕና የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፎርማት የሚመች አይመስለኝም። ምክንያቱም ሴራ ገብ፤ ኢጎ - ገብ ስለሆነ። የ6ኛው አገራዊ ምርጫ ተካሂዷል። ተጫኝ ሁነቶች የተደራጄ ቀውስ ግብዓቶች የፍርሃት፤ የስጋት፤ የጭንቀት ጫና ነበር። ከዘንድሮ ግን የተሻለ የነበረ ይመስለኛል። የ7ኛው አገራዊ ምርጫ #ምደባ ነው። ብልፄው ሁሉንም ተቆጣጥሮ በሥሩ ያስተዳደረበት እና ቦታወችን አቅዶ የደለደለበት ሁኔታ ነው የታየው። ውጤት ለመንገር መዝግየቱም ለዚያ ነው። ፌስታውን ተመልክቻለሁኝ። ይህ አይጠቅምም። እራስን መሸንገል ስለሚሆን። ዕውነትን ሳይሸሹ በዕውነት ልክ እራስን አርሞ ወደ ትክክለኛው ኃላፊነት እና ተጠያቂነት መግባት የተገባ ይመስለኛል። ዕውነት ቅርፊት አይደለም እና። ስኬት ቀጣይነቱ በዕውነት፤ በፋክት አቅም ስለሆነ። በሻሻ ላይ ምርጫ ተካሄዷል። ጠቅላይ ሚሩ አሸነፋ ያስኬ...