ልጥፎች

ብራቮ ፕሬዚዳንት ሩቶ በዓለም ቁልፍ የሰላም ጉባኤ በልቅና መመረጥ መታደል! ተስማምቶኛልም።

ምስል
  ብራቮ ፕሬዚዳንት ሩቶ በዓለም ቁልፍ የሰላም ጉባኤ በልቅና መመረጥ መታደል! ተስማምቶኛልም። "የቤትህ ቅናት በላኝ።"     ዬአቤቾ ሃቅ እና ሳቅ ሚዲያ ሳዳምጥ "የኬንያን ውክልና በዓለም ሰላም ላይ አቅሎ አቅርቦታል። ደሬ ዜናውን እንደሠራውም አደመጥኩ። ደሬ ዜናውን ሲሰራው የኢትዮጵያ ደረጃ መወሰድ "የቤትህ ቅናት በላኝ" ብሎ ሊሆን ይችላል ብዬ አስባለሁ። ኬንያም የእኛ ብትሆን ግን እንደ ፓን አፍሪካኒስት አንከር አገር ግን ኢትዮጵያ ደረጃዋን ማጣቷ የደሬን የዜናውን ትክክለኝነት ለእኔ ይገልፅልኛል። አቤቾ ሃቅና ሳቅ ለምን የጠሚር አብይ አህመድን ዜና አትዘግቡም ዓይነት ሃሳብ አቅርቧል። የመንግሥት ሚዲያ እነ ሉዓላዊ፤ እነ ሃቅ እና ሳቅ ወዘተ ምን ይሥሩ። ሌላ ሥራ ምን አላቸው? አሸበረቅን ነው። በሚቀጥለው ዓመት ተመንድገን የታንኪው ዘመን ይሆናል ነው። ያድርገው። የሆነ ሆኖ አይደለም የኢትዮጵያ ዜና ዘጋቢወች ዓለም አጀንዳቸው እኮ ኢትዮጵያ ነበረች። #በአወንታዊነት ። የፕሬዚዳንት ኦባማ ወደ ሥልጣን የመጡበትን ዘመን የሚመጥን ብቁ አትኩሮት ነበር። ለምን አሁን ለሚለው #ችግሩን ማጥናት #ለመፍትሄው #መቁረጥ ይገባል። በውነቱ የዓለም የአገር ውስጥ ተፈናቃይ ሻንፕዮን ለሆነች አገር፤ ሁለት ቤተ - መንግሥት ላላት አገር አዲስ እና ጎንደር ሌላ ቤተ - መንግሥት መሥራት ያስፈልጋታልን? #አሁን #ዛሬ ? የዓለም የሰላም ሎሬት ለዛውም አፍሪካ ላይ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ እያሉ #ሦስተኛው ዓለም ጦርነትን ያሰጋውን አርማጌዶን የራሽያ እና የዩክሬን፤ የኔቶ እና የራሺያ ጦርነትን ለመክላት በሚካሄደው ግሎባል ጉባኤ ለዛውም በቅድስት አገር ሲዊዘርላንድ #የኢትዮጵያ #አሻራ #ነጥፎ ተንኩሳን የማታውቀው የአክባሪያ

ታግቶ ያለው ሰባተኛ መጽሐፌ።

ምስል
      ታግቶ ያለው ሰባተኛ መጽሐፌ። አጋቾች ቆላልፈው ሳይፈቱት ተነኑ። ቀሪወች ጥገኛ??? እኛም በገዳማችን ተቆጥበን ዕድሜ ለአጤ ፌቡ አለን። ዝቅም መንጠራራትም ሳያሰኜን። ጎንደሬወች ባለ ቅኔወች ናቸው። "ልክን ማወቅ ከልኩ ያደርሳል ይላሉ። " ሆንበት። አለንበት። አለንለት ለቅኔያችን።

ኢትዮጵያን የማበጀት አቅም የነበራቸው የአገር ብራንድ ናቸው ያሳደጉኝ

ምስል
  የሲዊዝጀማሪ ጋዜጠኞች፤ ጀማሪ ፖለቲከኞች ይገርሙኝ ነበር። ሥነ ፁሁፍም፤ መምራትም፤ ሚዲያም፤ ፖለቲካም እዚህ ሀ ሁ ያልኩ ይመስላቸዋል። እንደ እኔ ዕድለኛ የለም። በሁሉም ኮርስ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን የማበጀት አቅም የነበራቸው የአገር ብራንድ ናቸው ያሳደጉኝ። እናም ምን እንዳለኝ አውቃለሁ። ምን እንደለለኝም። ምን እንደሚፈቀድልኝም፤ ምን እንደማይፈቀድልኝም የመብቴን ጣሪያ እና ግድግዳ አውቃለሁ። እኔ በእኔ ውስጥ መኖርከተሳነው፦ እኔ እኔን ማሰናበት አለበት። ይህ ደግሞ በሥርጉትሻ የማይታሰብ ነው። የእኔ የምለው ራዕይ፤ ፍልስፍና፤ ዓላማ አለኝ። ዛሬ ፖዘቲብ ኢነርጂ ስለሚባለው እኔ የተከበሩ የተመድን ዋና ፀሐፊ ደጉን አቶ ኪም፤ የአውሮፓ ህብረትን ፕሬዚዳንት የዛሬ ዘጠኝ ዓመት ዓለም አስፈራችኝ ክፋነትን ሊቋቋም የሚችል ተቋም ይፈጠር። የፍቅር ተፈጥሮ፤ የህግ ተፈጥሮ ካሪክለም ተነድፎለት ሁሉም ይማረው ብዬ ሞግቻለሁ። መልስም ተልኮልኛል። እና ሞገደኛውን ሥርጉትሻ ህሊና ላይ ቁብ ብሎ መሾፈር አይፈቀድም፤ አልተፈቀደምም ወደፊትም። በንፁህ ህሊና በነፃ ህዝቤን አገልግያለሁ። ወደፊትም። ላይ ላዮዋን ነው። ብዙ እጅግ የተከደኑ ዕንቁ ተግባራትን ለአገሬ ዕጣ ነፍሴን ፈጽሜላታለሁ። ቀረ ጎድሎባታል የምለው የለም።ፈጽሞ። ለዚህም ነው በቁጥብነት ገድሜ እምኖረው። ሥርጉ// ሰብለ ሕይወት ውቦቼ እረገት ይሁን። ደህና ሁኑልኝ። አሜን። "የሰው ልብ መንገድ ያዘጋጃል እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።" (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱)