ልጥፎች

እቴጌ ጎንደር።

ምስል
 

የፔጄን ህግ መጠበቅ ግዴታ ነው። ዘለፋ እና ማዋረድም #ማቆም ግዴታ ነው።

ምስል
  የፔጄን ህግ መጠበቅ ግዴታ ነው። ዘለፋ እና ማዋረድም #ማቆም ግዴታ ነው።   "ህግ ተላላፊወችን ጠላሁ።"   ከእኔ ፔጅ ላይ #silent Discrimnation & #silent Emotional neglation ፈጽሞ አይፈቀድም። ዛሬ በውል ተደራጅተው የመጡ የዚህ ስሜት ተጋሪወች ቤታችን አጉድፈውታል። ሃሳብን አቅርቦ በሃሳብ እኔን መሞገት ይቻላል። አቅሙ ከኖረ። በስተቀር ግን በሰው ልጅ በገጽ አቀማመጥ፤ በዕድሜ፦ በፆታ፤ በሃይማኖት፤ በቆዳ ቀለም ምንም ዓይነት ተጽዕኖ ለማሳደር መሞከር ፈጽሞ አልፈቅድም።   በተጨማሪም ስድብ፤ ማዋረድ፤ ነውረኛ ቃላትን እና ሐረጋትን መጠቀምም አልፈቅድም። ለምን ብቻዬን አልቀርም። አይደለም ከእኔ ፔጅ በጓደኞቼ፤ በተከታዮቼ ፔጅ ላይም #ነውረኛ ነገር ካዬሁ መልስ አያስፈልግም #መራራ #ስንብት ይሆናል። ጋዜጠኛ፤ ፀሐፊ እና ሞጋች አቶ ታዲዮስ ታንቱ ወገኔ ናቸው።   በዚህ ዕድሜያቸው #በበቀል #መቀጥቀጣቸው ውስጤን ያሳምመዋል። በማረፊያቸው ጊዜ፤ በመመስገኛ ጊዚያቸው እንዲህ #የካቴና #ቀለብ ሲሆኑ እንደ ትውልድ ያንገበግበኛል። የማይስማማ ሃሳብ ካነሱ መሞገት እንጂ ሥልጣን አለኝ ተብሎ እንዲህ #በበቀል ማንገላታት የተገባ አይደለም።    ስንት እና ስንት አገር እና ትውልድን ማኒፌስቶ ነድፈው #ገዝተው ፤ #ገድለው ፤ #አስረው ፤ #አግተው ህዝብ #አሰቃይተው እንኳን በሰላም እዬኖሩ ነው። ማንም ፍፁም አይደለም። ግድፈት ተፈጥሯዊ ነው። የማይገድፍ #ዕቃ መሆን አለበት። ግድፈት እንኳን ቢኖር በዚህ መልክ መበቀል #የሥልጣኔ ማነስ ነው። በሌላ በኩል #የበታችነት ስሜትም ነው። በራስ መተማመን ሲያንስ #ምቀኝነት ፦ #ቅናት እና #በቀለኝነት አይቀሬ ነው።   ለዛውም አገር እዬገዙ ህዝብ እያስተ

ጎርፍ ሥራ አይበዛበትም መንገድ ላይ ያገኜውን ዝባዝንኬ ያግበሰብሰዋል። ጊዜ ቴርሞ ሜትር ነው። ዘመንም እንዲሁ። ግን አንጎል ብቻ ሳይሆን ህሊና ላላቸው ብቻ። አንጎልማ ድንቢጥም አላት።

ምስል
      #እንደ ጥንቸል #የመሞከሪያ #ጣቢያ ኢትዮጵያ። ይህን የዛሬ 13/14 ዓመት የተናገርኩት፣ የፃፍኩበት ነው። የዛሬ እንዳይመስላችሁ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 28/07/2022   #መንግስት #የሸፈተባት #አገር - #ኢትዮጵያ ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 28/07/2022   ዘመን ለራሱ በራሱ #ቴርሞ #ሜትር ነው። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 28/07/2022   ኢትዮጵያ በብዙ ሁኔታ #ከብዳናላች አንዱን ይዘን ሌላውን #ጥለን መገስገስ የብልህነታችን ልኬታ ዝቅታ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 28/07/2022   ምንጊዜም ማዕረግ፣ ምንግዜም በሞገስ ለሚገሰግሰው የአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ #ህሊና #ለጎጃም አማራ። በዛ ክፋ የህወሃት ዘመን #ራሱን #የሰጠ ፣ በዚህ ምፃዕትም #የተቀቀለ ። ጽላት! ሥርጉተ©ሥላሴ   ምንጊዜም ማዕረግ፣ ምንግዜም በሞገስ ለሚገሰግሰው የአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ #ህሊና #ለጎጃም አማራ። በዛ ክፋ የህወሃት ዘመን #ራሱን #የሰጠ ፣ በዚህ ምፃዕትም #የተቀቀለ ። ጽላት! ሥርጉተ©ሥላሴ   በውስጡ ከሌለህ በምትፈልገው ውስጥ የሞቀ ቀለም ቀቢ ብቻ ትሆናለህ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 28/07/2022  ተስፋህ በሰከነ ቋሚ ተግባር እንጅ በልዝ እንጨት ውስጥ አታገኘውም። ልዝ እንጨት ወይ #አይነድ ፣ ወይ ደግሞ #አያነድ ። የራያችን መጓጎል ብልኃቱ ጠፍቶን። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie   ተስፋህ በሰከነ ቋሚ ተግባር እንጅ በልዝ እንጨት ውስጥ አታገኘውም። ልዝ እንጨት ወይ #አይነድ ፣ ወይ ደግሞ #አያነድ ። የራያችን መጓጎል ብልኃቱ ጠፍቶን። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  ጊዜ ቴርሞ ሜትር ነው

አንድ የምታውቁት መልካም ሰብዕና በድንገት እራሱን አጥቶ ከደግነት አስተሳሰቡ ወጥቶ #ክፋነትን ተደላደልብኝ ሲል #አትደንግጡ።

ምስል
  አ ን ድ የምታውቁት መልካም ሰብዕና በድንገት እራሱን አጥቶ ከደግነት አስተሳሰቡ ወጥቶ # ክፋነትን ተደላደልብኝ ሲል # አትደንግጡ ። " ሽበትስ የሰው ዕውቀቱ ነው፦የእርጅናም ዘውዱ ያለነውር መኖር ነው። " ( መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፱ ) እንዴት አደራችሁ ማህበረ - ቅንነት። ጎፋስ አማራ ክልልስ እንዴት አድረው ይሆን ????    # አለመደንገጡ በብዙ ይረዳል። ምክንያቱም # እንድትረጋጉ ያደርገል። የሰው ልጅ ሲፀነስ በፈጣሪው ንጽህና፦ ቅድስና፤ መባረክ ልክ ነው ብዬ አምናለሁኝ። ቅድስናው፤ መባረኩ ፈተና የሚገጥመው ከተወለደ በኋላ ነው የሚል ዕምነትም አለኝ። ከተወለደ በኋላ # ለምን ? ንጽህናውን፤ ቅድስናውን ሊያስቀጥል የሚችል ተቋም ዓለማችን ስለአልሰራች። በዚህ ዘርፍ ዓለማችን ልሙጥ ናት። ስለዚህ ክፋ ሃሳብ ሙሉ ለሙሉ፤ ወይንም በከፊል የሰው ልጅ ከተፈጠረ በኋላ # ይሞግተዋል ። እራሳቸውን ያሸነፋ ጀግኖች ሊኖሩ ይችላሉ። እነሱ ግን ጥቂት ናቸው። ጥቂት መሆናቸው ብቻ አይደለም። ጥቂቶችም ውሎ ሲያድር ከክፋነት ሃሳብ ጋር ሊላመዱ ይችላሉ። በተለይ ሙሉለሙሉ በክፋ ሃሳብ ሙሉ # የተነከሩ የቅርብ ሰው ካላቸው ቀስበቀስ ዝንባሌያቸው ወደዛ ይሆናል። 1) ክፋ ሃሳብ # ፈጣን ነው። 2) ክፋ ሃሳብ # ወራሪም ነው። 3) ክፋ ሃሳብ # ተስፋፊም ነው። 4) ክፋ ሃሳብ # ተጫኝም ነው። 5) ክፋ ሃሳብ # ሰልቃጭም ነው ። እንደሚታወቀው የክፋ ሃሳብን ወረራ፤ የክፋ ሃሳብን መስፋፋ