ልጥፎች

የአማራ ህዝብ ከቶ ወደ #ማርስ ይምጠቅላችሁን?????? ሞፈር ቀንበርን ለምን #ታነዱታላችሁ??? የአማራን #ገበሬ ለምን #በድሮን ታነዱታላችሁ? መሬቷንስ ለምን #በቦንብ መርዝ ታነዟታላችሁ? "የቤትህ ቅናት በላኝ።"

  የአማራ ህዝብ ከቶ ወደ #ማርስ ይምጠቅላችሁን?????? ሞፈር ቀንበርን ለምን #ታነዱታላችሁ ??? የአማራን #ገበሬ ለምን #በድሮን ታነዱታላችሁ? መሬቷንስ ለምን #በቦንብ መርዝ ታነዟታላችሁ?    "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   እህል አልባ መኖር አለን? ዘር አልባ የሰው ልጅ ይቀጥላልን? ውኃስ አልባ መተንፈስ ይቻል ይሆን?    የኦነግ ጠረን የተላበሰው የኦህዴድ ወራሽ ብልጽግና የአማራ መሬት ይመረዝ ዘንድ ተግቶ እዬሰራ ነው። ለትውልድ እንዳይደርስ አርቆ በማሰብ ጠፍ የማድረግ ብቻ ሳይሆን በተመረዘ መሬት የሚበቅል አዝዕርት ለትውልድ የአካል አፈጣጠር እክል ይሆናል። #ገበሬን በቦንም?    ገበሬን በአውሮፕላን #መጨፍጨፍ ? ምን ይባል።    በአማራ ህዝብ ተገድሎም፤ ተዘርፎም፤ ተገሎም፤ ታስሮም፤ ተሰውሮም፤፦በገፍ በዬተገኘበት ተጨፍጭፎም የተረፈው በራህብ ያልቅ ዘንድ የጠቅላይ ሚር አብይ መንግሥት ተግቶ እዬሠራበት ይገኛል። የምርት ሰዓት፤ የእርሻ ወቅት ጠብቆ ይቀጣል ያሳዳል። ሲያሻውም ሰብሉን መስክ ላይ የዶግ አመድ ያስደርጋል። የአገር ልጅነቱን ፍቆ የውጭ ወራሪ ነው የሚመስለው። መሃከነ።    የሚገርመኝ አብረው የሚሠሩት የአማራ ግዑዛን ናቸው። ህሊና የሚባል ያልሠራላቸው #ገደላገደሎች ። እኔ የገበሬ አደራጅ ነበርኩኝ። በአንድ ወቅት የኢትዮጵያን መሪ በአካል አግኝቼ ነበር። እናም መልሼ ላላገኝሽ እችላለሁ እና ምን ላድርግልሽ ሲሉ በትህትና ጠየቁኝ። ጎበዝ ተማሪ ነኝ። ውጭ አገር ለትምህርት ላኩኝ አላልኩም። ወይንም አዲስ አበባ የተሻለ ሥራ ይሰጠኝ አላልኩም። ወይንም እዚህ ሥራ ይሰጠኝ አላልኩም።   የጠዬቅኩት ገበሬ መንደር ሄጄ ገበሬ ማደራጀት ነው እምፈልገው አልኩኝ። እኔ የጎንደር ከተማ ልጅ ነኝ። ቤተሰቦቼም ባላባቶች ስለሆኑ ገጠሩን

#አማራነትን አታሰቃዩት።

  #አማራነትን አታሰቃዩት።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   አቶ ቴወድሮስ የአብን አ መራር ነበሩ። ግልጽና ቀጥተኛም ናቸው። በሙያቸው በተመረቁበት መስክ ተደላድለው መሥራት ሲችሉ የእትብት ችግርን ልጋራ ብለው አብን ተቀላቀሉ። በጣም ደፋር የሆኑ አስተያዬቶችን በግል ሲያቀርቡ አስተውል ነበር። ከታሠሩ ጀምሮ በእሳቸው ዙሪያ የሚተጋ አንድም ቀንጣ ነፍስ አላዬሁም። ከስብስቡ የወል የመታገያ ምስልም የሉም። ለምን?   አይዋ አብን "አንድ አማራ ለሁሉም አመራ" ብሎ ሲያስፈነድቅ ምነው ለራሱ መሆን ተሳነው? ፓርላማም፤ ምክር ቤትም ተመርጠው የገቡ ወገኖቹ ለካቴና ሲዳረጉ ዝም። በቃ ዝም። አቶ ካሳ ተሻገርም ጠንካራ ሞጋች ናቸው።   አይዋ አብን ለሽ እንዳለ ነው። አሁንማ #መቅኖውን ለብልጽግና ቀላልቦ ዕጣ ነፍሱን እንደቀረ የሰሞናቱ የኢታማጆሩ ቃለ ምልልስ እርቃኑ መሆኑን አስገነዘበን። አያድርስ ነው። ያን ሁሉ አቅም #ሜዳ #አደር አድርጎ #በከንቱነት የቀረ #ጉደኛ ። የሆነ ሆኖ የአማራ ፖለቲከኞችን እያደኑ ማሰር ይቁም።    የአማራ ሕዝብ ኢትዮጵያዊ ነኝ ቢልም አሳር፤ አማራ ነኝ ቢልም ፍዳ። በእሳተ ጎመራ ላርባ የሚገረፍ፤ ቀጭወቹን ሃግ የሚል የጠፋበት ዘመን ነው። ያው ባለ ኮፒራይቱም ወዘተረፈ ስለሆነ በግል ለሚተጉ የእኔን መሰል ባተሌወች ጋዳ ነው። ዝም ስንል ደግሞ እንዲህ የሚረሱ፤ ጨርሶም የማይታወሱ ወገኖች ቁጥር በረከተ።   ለመሆኑ እነሱስ ቤተሰቦቻቸውስ በምን ሁኔታ ይገኙ ይሆን? ጤናቸውስ በምን ደረጃ ይገኝ ይሆን። ሙሉ ስድስት አመት በእስር መጋዝ። ምን ይጠና የአማራ ሕዝብ? ምንስ #ከብረት #ቁርጥራጭ #የተሰራ #ጽናት አደለው ፈጣሪ????    በዬደቂቃው፤ በዬሰከንዱ የሚታገተው፤ የሚታደነው፤ የሚገደለው፤ የሚሰወረ

የተከበረውን አቶ ኦባንግ ሜቶ አስመልክቶ ፀፀት የለብኝም። ይድረስ ለወዳጄ ለአቶ ኦባንግ ሜቶ። ከአለህበት። #ምዕራፍ ፲፬ "የቤትህ ቅናት በላኝ።"

  የተከበረውን አቶ ኦባንግ ሜቶ አስመልክቶ ፀፀት የለብኝም። ይድረስ ለወዳጄ ለአቶ ኦባንግ ሜቶ። ከአለህበት። #ምዕራፍ ፲፬ "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   #የአፋልጉኝ #ትሁታዊ #ጥያቄ ። #ጠይም #ዕንቋችን #እናፈላልግ ። #አቶ #ኦባንግ #ሜቶ የት ነው ያለው? ምን ገጠመው? ምንስ ሆነ? ታመመን?   እጅግ የማከብርህ፤ የምሳሳልህ ወንድሜ አቶ ኦባንግ ሜቶ በቀድሞው አጠራሬ #ኦባንግሻን ዶር ኦባንግ #ኢትዮጵያ በአያሌው እንዴት ባጀህልኝ? ባለቤትህ እንዴት ናቸው? መላ ቤተሰብህ እንደምን ነው? የምታፈቅራት ኢትዮጵያ ጠረኗ እንዴት እና እንዴት እያደረገህ ይሆን? ታድለኃል ልበልህ ይሆን? ጠቀሜታውን እምታውቀው አንተው ነህ።   ለመሆኑ ኢትዮጵያ እንዴት ናት? ያቀድከው #ተስፋስ ዕውን ማድረግ ችለህ ይሆን? የአውሮፓ ህብረት ሽልማት ሲያልፍህ በጣም አዘንኩኝ። ብዙ የተጋህ ድንቅ የሰባዕዊ መብት ተሟጋችም ነበርክ። ከመኪና አደጋ ከሞት ተርፈህ፦ ተድረህ፦ አገርህ ገብተህ በተወሰነ ደረጃ ከምታከብረው ህዝብህ ጋር #መሳቅህ ቢያስደስተኝም ለረጅም ጊዜ #ድምጽህ #መጥፋቱ ግን ሰርክ #ይጎሰጉሰኛል ።   የእኛ ውድ #ጠይማችን ዕንቁ አንተን የበላ ጅብ አልጮኽ አለ። አዲስ ዓመት መጥቶ ሲሄድ ድምጽህን መስማት አልቻልኩም። ለነገሩ ክቡር ኮነሬል ጎሹ ወልዴም አገር ሲገቡ ከነበረው ሴሪሞኒ ውጪ የት እንዳሉ፤ በምን ሁኔታ እንደሚገኙ መረጃው የለም። የተከበሩ አንባሳደር ካሳ ከበደም ከብዙ የዝምታ ጊዜ በኋላ በሥጋ መለየታቸውን አዳመጥኩኝ። ፀጥታ፤ ዝምታ። ጥሞና ታቅዶ ከተፈፀመ መልካም ነው። ተጫኝ እና አስገዳጅ ሁኔት ካልኖረ።   ታስታውስ እንደ ሆነ #ነሐሴ 2010 እንደ አገራችን አቆጣጠር #ተስፋችን #ተጠልፏል #የመንፈስ #ትጥቅህን አትፍታ ብዬ