#ጉግሱ #በአርጀንቲና አሸናፊነት ተጠናቀቀ።
#ጉግሱ #በአርጀንቲና አሸናፊነት ተጠናቀቀ። "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፱። ጉዳዩ ፖለቲካል ኢሹም የታከለበት ስለሆነ የመጀመሪያው የጨዋታ ጊዜ አየሩ አግሬሲብ ነበር። የማሸነፍ እና የመሸነፍ ጉዳይ ሌላ የውስጥ አጀንዳ ስለነበረበት ከበድ ይል ነበር። የሆነ ሆኖ ከግማሽ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በኋላ ቀድሞ እንግሊዝ ባስገባው ጎል ሌላ ትዕይንት ተፈጠረ። ውጤቱም የአርጀንቲና #ሁለት እንግሊዝ #አንድ በማግኜት በመደበኛ የጨዋታ ጊዜ ተጠናቀቀ። የመጀመሪያው ግማሽ የጨዋታ ጊዜ #አስፈሪ ነበር። አየሩ እራሱ አግሬሲብ ነበር። የአርጀንቲናው 17 ቁጥር ነገረ ሥራው ያስፈራ ነበር። በኋላ ተቀይሯል። አየሩ ረጋ ያለው፤ ትንሽ ሻል ያለው ከመጀመሪያው #ከውሃ እረፍት በኋላ ነበር። እስከ ውሃ እረፍት በነበረው ጊዜ በሁለቱም ተፋላሚ ቡድኖች ማህከል ግብ አካባቢ ሙከራ አድርገዋል። ከመደበኛ እረፍት በኋላ 54.27 ደቂቃ ላይ እንግሊዞች ከመረብ ጋር #የታረቀ አንድ ጎል አስቆጠሩ። ይህን ጊዜ አርጀንቲናወች አቅማቸውን ጨምረው ፍልሚያውን #አፋሙት ። አርጀንቲናወች ብዙ #የማዕዘን ምት ዕድል አግኝተዋል። በተጨማሪም የእጅ ኳስ ውርወራም ዕድል በስፋት ቀንቷቸዋል። ግን መረብ እና ኳስ ለረጅም ጊዜ #መታረቅ አልቻሉም ነበር። እንግሊዝ ቡድን አንድ ጎል #ቀድሞ ካስገባ በኋላ ግን በተከታታይ በእንግሊዝ መረብ ላይ አርጀንቲናወች ጥቃቱን ቀጠሉ። በተከታታይ እና በትጋት የእንግሊዞችን መደበኛ ሜድ ከበው ተከታታይ ጥረት አደረጉ። አሳኩም። አርጀንቲናወች በብዙ #አታካች ሙከራ #ላባቸውን ጠብ አድርገው በጥረታቸው የመጀመሪያውን የአቻነት ችቦ 85...