የሰማያዊ ፓርቲ የቆራጣ የኮፒ ራይት ሩጫ ተረኛ ነው ለፍጥጫ!

የጢባ ጢቦ የኮፒ©ራይት ሽሚያ እንደ ተለመደው።
„የነጎድጋድህ ድምጽ በአውሎ ነበር፣
መብረቆች ለዓለም አበሩ
ምድር ተናወጠች
ተንቀጠቀጠችም።
ምዕራፍ 72 ቆጥር 18

ከሥርጉተ ሥላሴ
18.07.2018
(ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)




  • ·       የእነ ጭልፊት ነገር ሞትለፍ ነው።

Ethiopia: የኢትዮጵያ ሰንደቀ አላማ መሀል ላይ ያለዉ አርማ እንዲቀየር ሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ አቀረበ

  • የዕውነቱ ዕንብርት በሚዛን!

ሰንደቅ አላማና የአማራ ህዝብ ስሜትንግሱ ጥላሁንና ቢቢሲ…. (አያሌው መንበር)
  • ·       ልሙዱ አቋራጭ።

ሌብነት እንደ ትልቅ የፖለቲካ ስልትና ስትራቴጅ እዬተለመደ መጣ። እኔ በሌላ ድርጅት እንዲህ ዓይነት ኩነት አይቼ አላውቅም። ሰምቼም አላውቅም። ምክንያቱም አነሰም በዛ የፖለቲካ ድርጅት ፈጣሪዎች ሃሳብ ይዘው ነው የሚነሱት እንጂ ሃሳብ ካለው እጣዳለሁኝ ብለው አገር ሲያምሱ እና ሲያተራምሱ ተገጥሞ አይታወቅም።

የአማራ ተጋድሎ እንደ መጣ በዚያው ሰሞን ተጨማሪ የራዲዮ ጣቢያ ተከፈተ የቅንጅትን መንፈስ እንጠራለን ተብሎ „ትሳንኤ ራዲዮ“ ትንሳዬ ራዲዮ ቅንጅንትን የደገፈ እና በፅኑ የረዳ ራዲዮ ዝግጅት ነበር፤ እኔም ለተወሰነ ጊዜ እርጅን ብለውኝ ሰርቼ ነበር።

አሁን ታሪክ እራሱን ይደግማል እንዲሉ የሰሞኑ አቤቱ ሰማያዊ ጥድፊያ ደግሞ ይሄው ነው። ሰማያዊ አዲስ አስቂኝ ጉዳይ ለኢትዮጵያ መንግሥት እንዳቀረበ አዳመጥኩኝ። የእነ ጭልፊት ነገር የህዝብ ድጋፍ ከሚገኘው ቦታ ላይ ሰው አፈላልጎ በመሳጥ ነው። 


ይሄ የሆነው በተለያዩ ምክንያቶች ነው አንደኛው እንደ ተለመደው ይሄን „ካሉት ይሻሉ በማለት ብቻ ሳይሆን የነጭ አደራዳሪ ካልመጣ“ በጅ አልልም ብሎ በገረጀጀ አቋሙ አዬሩን ሲያውከው የባጀው ኩፍሱ ሰማያዊ ሳያስበው፤ ሳያልመው የሚሊዮኖች ድምጽ ለአብይ ሲሆን ደንግጧል።


ለአዛጋጆች የነበረው የሚዲያ ሽፋንም ርድ አስይዞታል፤ መቼም ያቺ የሚሊዮን የፍቅር የራስ መርዘን ሳይሆነ የሆድ መርዘኑ ያልተነሳ አይኖርም ህልመኛው ሁሉ እንኩት ያለበት ዕለት ስለነበረ፤ አስከ 5 ሚሊዮን ህዝብ ነበር በአፍሪካ መዲና የተገኘው። የባህርደሩ እና የሌሎች ከተሞች ሲታከለሉማ የትዬሌለ ነው። መንፈሱ ራሱ ጽናትን እንዴት እንደ ለገሰ። መተማመንን እንዴት እንዳነፀ፤ ሃይልን እንዴት እንደያዬዘ።

አሁን ጉዳዩ ሰማያዊ እራፊ መሬት የመንፈስ መለቃም ነው፤ ያው ይህን የተማራው ከታዘለበት መንፈስ ነው። ከተፈጠረ ሰማያዊ እንዲህ ሲያውክም በጠራራ ጸሐይ የሚሊዮኖችን መንፈስ በሽንጥ ገብቶ ሲዘርፍ አይቼ አላውም፤ በራሱ ጉዳይ ነበር ሲታመስ ሲከፍል የከራረመው እስከ ፕ/ አስራት ወልደዬስ የመንፈስ ወራራ ድረስ። 

ወደ ቀደምው ምልሰት ሲሆነ የ አሁኑ የድጋፍ ሰልፍ የ አማራ የተጋድሎ ዓርማ እን መንፈስን አጉልቶ ሰንደቁን ይዞ ሰልፈኛው ስለወጣ፤ አሁን በጥድፊያ ያው በተመደው ሸልከህ ግባ ጥበብ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጠ።

ትንሽ ሰነባብቶ ደግሞ እኔ ነበርኩ ይለናል እስተ እጮኛው ድረስ … የእኛ ሰዎች ነበሩበት አይቀሬ ነው፤ ተረበኞች። ውሸት ክብራቸው ነው። አንዱ ውሸት ሲነፍስበት ቃል ለተጋበለት ደጋፊ ሌላ ደግሞ ኦርጅናሉ ይከሰታል፤ ያው እንደ ተማጠ ተመሽቶ ይነጋል፤ ቀዳዳ ውተፋው። ያ ክስተት ደግሞ ተጋጭቶ እና አጋጭቶ ይከስማል … ቅጥፈት ነው ነፍሳቸውን እስተዚህች ቀን ድረስ ያቆዬችላቸው ናት።


ሁለተኛው ደግሞ የሰንደቁ ይህን ያህል በህዝብ ውስጥ ተምስጥሮ በተለይ ከአማራ ክልል ውጪ ይኖራል ብሎ አልገመተውም ነበር ሰማያዊው፤ ሰንደቅዓላማው የህዝብ ፍቅረኛ መሆኑ ቢታወቅም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ይሆናል ተብሎ ስላልተገመተ ስለ ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማው አቤቱ ሰማያዊ ፓርቲ አጀንዳው አደረገው ተብሎ፤ የጵጵስና ቆብ ለመድፋት ነው። አውራ ተሁኖ ለመውጣት።

ሲወሰነም እኔ አስደረኩት በማለት እሱን ከልብ ህዝብ እንዲቀበለው መቅደሙ ነው። ሸቀጥ በመሸቀጥ የህዝብን መንፈስ መግዛት አይቻለውም! በቃል ባሉት በቃዱት ሞጥሮ ማትብን ጠብቆ በመገኘት እንጂ እንደ ተልባ ስፍር በማዋለል የሚታፈስ የመንፈስ ሃብት የለም። ፖለቲካ ትርፉ በደከምክለት ዕውነት ውስጥ ነው የሚታፈሰው። በለፋህበት መስኖ ውስጥ ነው የመታፈሰው።


አቤቱ አንዲሱ የቤተ መንግሥት ነጭ ለባሽ ይህ ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ አገር ውስጥ ይህን ያህል ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆኑ ያለወቀው ጉዳይ ነው። ያው ሰማያዊ ጤና ስለነሳው የወረሰውን ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች መልቅም ከጀማመረው ሰንባብቷል።

ጦማርያን እና ቀረብ ይላሉ የተባሉትንም … የ አሁኑ መስመር እራሱ በምን ስሌት እና ቀመር ስመሆኑ ምርምር ተደርጎበታል። በድካም የሚገኝ ውጤት እንጂ በ አማላጅ የፖለቲካ ድልድይ አይሰራም። ይህ ውርስም ሊሆን አይገባም ነበር። አብሶ በወጣት ፖለቲከኞች። ዛሬ ያልሠሩ ወጣት ሊሂቃን፤ ዛሬ አዲስ ሃሳብ ያላፈቀሉ መቼ? ሲያሩጁማ እንደ እነ አቦይ ምርኩዝ ነው በቃ …


ደግሞ መጠመን በምልዕት የደም ግብር መጥመልመል ያሳፍራል። እጅግ ያሳፍራል። በሴራ ውስጥ ያለ ድርጅት ለዛውም ወጣት ተሁኑ … ተመስገን የሚባለው ዓራት ዓይናማ ሙሴዎች በህብረ ቀለማት አሉ። የናቁት ይወርሳል ሆኖ የዓለም ሚደያም አምደኛ ሆነዋል።
         ጎንደር ደብረብረብርሃን የሃምሌ ስላሴ ሲከር።

  • ·         ባለ ኮፒ ራይቱ አንበሳው አለ፤ አለሞተም አልታመም!
ይህን ሰንደቅ ዓላማ በድፍረት ይዞ አደባባይ የወጣው ከምንም ይደርሳል ተብሎ ያልተገመተው፤ ዬትኛውም ፓርቲ አጀንዳው እና ጉዳዩ ያልነበረው የወልቃይት ጠገዴ የአማራ የማንነት ተጋድሎ የሐምሌ 5 አብዮት ነው፤ ይህን ድል ያስገኘው ከዚህ የድል ቀን ቀጥሎ በተካሄዱት አማራ መሬት ላይ ሰንደቁ ክብሩ ተመልሷል ከሁለት ዓመት በፊት።


              
ዛሬ ጭራ ላይ የኖረው ራሱን ለማቆም ተስኖት በራሱ ፍርሻ ላይ ሌላ ጋብቻ ያማረው ሰማያዊ ቀንድ ነኝ ብሎ እንደ ግርፉ ይህን ውርስ አድርጎ ቀርቧል።

አለቃው ድርጅት ግንቦት 7 ተጋድሎወን ለመቀማት፤ ካልቻለም አዳፍኖ ጨቁኖ ለማሰቀርት ንጹህ Discrmnation እስከ ሚደያው እስከ ኢሳት ድረስ አካሂዶ፤ ግን እራሱን ያደነው ጭንቅላቱን ያሰፈታለት የዛ ተጋድሎ መንፈስ ሆነ ተገኘ። አዙሮ ያ ገድለኛ መንፈስ ከእጁ ጣለው፤ እሱም አይሆኑ ሆኖ የውሽማ ሞት ሆነ ነገር ዓለሙ።



ክሱን ሁሉ ያስናሳለት የዛ ተጋድሎ መንፈስ ሆኖ ተገኜ። ይህ የእዮር ድንጋጌ ነው። የአማራ መንፈስ ማለትም ምን ማለት እንደ ሆን በጋህዱ ዓለም ታምራቱ የታየበት ልዩ ምስክራዊ ዘመን ነው።

ንጹሁን ባንዴራ ዛሬ የሁሉም ዓርማ ሆኖ በዬድጋፉ ሰልፍ እንዲወጣ ያስደረገው የዛ ለጉልበተ፤ ለህይወቱ፤ ለታሪኩ፤ ለድካሙ፤ ለፍቅሩ፤  ለአክብሮቱ፤ ለቅንነቱ የማይሳሳው የአማራ አምላክ/ አላህ ያደረገው የሰማይ ታእምር ነው።



ከዚህ ባሻገር በውጭ አገር ስብሰባዎች ሆኖ በማያውቅ መልኩ እናት ድርጀቱ ግንቦት 7 ስብሰባዎችን ሁሉ ያዥጉረጎረው እሱ ነበር። የቄሮን ልብ ለመግዛት የኦንግን ዓርማ አዝሎ ተሸከሙልኝ ሲል የባጀው።



ይህም ብቻ አይደለም የአማራ ታታሪዎች የጎንዮሽ ቃለ ምልልስ ሲደረግላቸው የአማራ ታገድሎ ሆናችሁ እንዴት አዳራሻችሁ በሙሉ ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሆነ ሁሉ ተብለው በኢትዮ ዩቱብ ተጠይቀውበታል። ተከሰውበታል።

እስኪዚህ ድረስ የሚሄድ ገመና ነው ያለው … አሁን ደግሞ የነፍጠኛው አርማ አሸናፊ ሆኖ ሲመጣ በሽንጥ ተመጣ። ከአማራ መንፈስ ተወጥቶ ወፊቱ አታወጣም። እርግማን አለበት። ንጽህናው ልክ ስሌለው፤ ሰው ሲያምንም ደንበር ስለሌለው … ሁሉ ነገር ህሊናውን በገፍ ነው የሚሸልመው። አይቆጠር አይሰፈር … 
ባህርዳር!


በሌላ በኩል ደግሞ አማራ የመንፈስ ዘራፊም ነጋዴም አይደለም። በፍቅር ውስጥ የንግድ ህግ አንደሌለ ጠንቅቆ ከነፍሱ ያውቀዋል አና። ትዕግስቱ ሲያልቅ ደግሞ ፍቅርን ፈቅዶ ያሰድደዋል። ቁርጥ ነው ውሳኔው አማራ። ወለም ዘለም የወለሌ ገበታ የለም።

የሆነው የግንቦት 7 የጡት ልጁ አቤቱ ሰማያዊ ፓርቲ የአማራ ይህልውና የተጋድሎውን ዕንብርት ጉዳይ እኔ አሰፈጸምኩት ለማለት ለመንግሥት ጥያቄ ቀረበ የሚል ዜና አስደመጠን። የጮሌዎች መንገድ ይሄው ነው አቋራጭ ሥም እና ዝና ለዛውም ባለመብቱ ደፋሩ የአማራ ተጋድሎ ሳይጠዬቅ። 

በድርጀት፤ በህዝብ ሃሳብ እና ድርጊት ላይ ሄዶ መለጠፍ፤ መሰርነቅ፤ የጉሮሮ አጥንት መሆን በቃ ብልሃት የሌለው ቅላት። ሌላ የግጭት ዓውድ ደግሞ መክፈት፤ ማስከፈት። እኛን የሚያስረሳ ያምጣላቸሁ ... 

የ አማራ ተጋድሎ ሰማዕት!


  • የግጭት ሽውታ…  

አቅም ለግለግ ብሎ ሲወጣ ወይ መቀማት፤ ወይ መዋጥ ወይ ደግሞ መዝረፍ። ይህ በማን እና በምን መሰላልነት እንደሆነ እናውቀዋለን … ተሎ በሉ ሰባራዋ አንካሳዋ ወፍ ሳትቀድማችሁ ስለመባላችሁ ጠንቋይ አያሰፍልገንም። የጉዞውን አንጀት ጉበቱን ለመድነው እኮ ተኖረበት … 

ከአማራ ተጋድሎ በፊት የእንጂነር ይልቃል ሰማያዊ ብዙ የተቆራረጡ መንፈሶቾን አገር ቤት ለማያያዝ ሞክሯል አብሶ የሴቶች የመጀመሪያውን የጣይቱን ሰላማዊ ሰልፍ አዲስ አባባ ላይ አካሄዷል፤ የሊቢያ ሰማዕታትን የሃዘን ቀን ለማሰብ ጥሯል፤ የአንድነት ፓርቲም በሚሊዮኖች ድምጽ እና በልሳኑ እጅግ በርካታ የህዝብ ማነቃቂያዎችን ፈጽሟል፤ በተከታታይ እና በቋሚነት የዘለቀው የወያኔ ሃርነት ትግራይን ይነቅለዋል ተብሎ የተተነበዬለት „የድምጻችን ይሰማ“ ወደር የማይወጣለት የተጋድሎ ስልታዊ ሁኔታዎች ሁላችንም አስደምሞናል። 



እነኝህ ሁሉ ግን አንድም ቀን ደፍረው የታሰረውን የነፃነት ዓርማ አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማውን ይዘው የመውጣት ድፍረት አልነበራቸውም። በፍጹም።

አማራ መሬት ላይ የተካሄዱ ተጋድሎዎች፤ የደብረታቦሩ፤ የባህርዳሩ፤ የማርቆሱ፤ የዳባቱ፤ የአንባ ጊዮርጊሱ የትናንሽ ከተሞች የነፃነት ተጋድሎዎች ግን ብሄራዊ ሰንደቄ ይሄ ነው ብለው እጅግ በድፈርት መድፍ እዬረገጡ፤ ካቴና ሳይፈሩ እጹብ ድንቅ ተጋድሎ እድርገዋል፤ የሳይጣኑን ምስል እያወረዱ የደማቸውን ዓይነት በጀግንነት ክብር ሰጥተውታል።

የዓውደ ዓመት ውሎዎች ሁሉ በዚህ ብሄራዊ ሰንደቅዓላማ የተዋቡ ነበሩ። እሰሩም፤ ግድያውም፤ እንግልቱም፤ መከራውም፤ መሳደዱም፤ አካል መጉደሉን አልፈራውም የምልዕት የአማራ ድምጽ።

የአማራ ሸባላ ለመንፈሱ አንድ ነው ልቡ! ዘመንም ጊዜም ከቃልኪዳኑ ጋር አያፋታውም።


ብሄራዊ ሰንደቅዓላማውን የወደዱ እንደ ለበሱት 20 ሺህ እሰረኛ፤ ባህርዳር ከተማ ላይ ብቻ 50 ንጹሃን፤ አንባጊዮርጊስ ከዛች ፍጹም ደሃ ከተማ 26 ህጻናት ለዛውም ከሱዳን ወታደር በመጣ ተጨፍጭፈዋል። ሰማዕትነት።
አስተረዬም ወሎ ላይ በባሩድ ጢስ ተስተጓጉሏል፤ አማራ ከሰንደቁ ፊት ቀድሞ ወድቋል፤ ባህርዳር ኮንሰርትም ሁሉ ያዬው ነው። የሰሞኑ የድጋፍ ሰልፍም ባህርዳር ላይ ኢትዮጵያ መሬት ላይ ተሠርቶ የማያወቅ ትንግርት ተሠርቷል። 


ደብረብርሃን ላይ ጎንደርም ወሎም በዬትናንሹ የአማራ ከተሞች የተካሄዱ የድጋፋዊ ሰልፎች ትንሽዬ ቻግኒ ሳትቀር ይህን ሰንደቅ ያከበሩ ከዚህ ውጪ ሌላ አንቀብልም ብለው ያመጹ ነበሩ።የመስቀል ደመራ ባዕልም እንዲሁ።
ጎንደር ከተማ ቢያሳ!

አሁን አቤቶ ሰማያዊ ኮፒ ራይቱ የእኔ ነው ሲል ሙልጭ ያለ ሌብነቱን በአደባባይ አውጥቶልናል፤ የተለመደ ነው ዝርፊያ በውርስነት አስቀጥላለሁ ባይ ነው አዲሱ የከብር ባለ ሊሻን።

ነገ ደግሞ ኮራ ደልድል ብሎ ተግባር አንድ ብሄራዊ ሰንደቄን አስከበርኩ ቁጥር ሁለት ደግሞ እንዲህ እንዲያ እያለ አውራ ዙፋን ያስደፋልናል። ሰው ያልነበረበትን፤ ያልዋለበትን፤ ያልደከመበትን በዬተገኘበት ሁሉ የእኔ ነው በአደባባይ እና በጠራራ ፀሐይ ዘረፋ እጅግ ያሰፋራል፤ ውርዴትም ነው።



ስለቴዲ አፍሮ ኮንሰርት በግልጽ ብአዴን በብሮድ ካስት ባለሥልጣናት በውስጥም መስመር ስንት ሙግት አካሂዶበታል፤ በይፋም ተከሶበታል እኮ አቶ ንጉሱ ጥላሁን እንቅጩን በድፍረት እና በልበ ሙሉነት  በአደባባይ መልስ ሰጥተውበታል። 


በሰሞኑም ጉዳይ ለቢቢሲ ለቀረበላቸው ጥያቄ መሰሉን መልስ ሰጥተውበታል፤ ከላይም ማያያዠውን ለጥፌያዋለሁኝ።
በማህል አዲሶቹ ጮሌዎች የመንፈስ ዘረፋ የማይጠቅማቸው እነ አጅሬ ተሰነቀሩ የግንቦት 7 ጸበለ ጻዲቅ እንዲህ ነው … መለጠፍ፤ ደምቆ የወጣውን መጥለፍ፤ የኔ ነው ማለት፤ ሌብነት ትልቁ የፓለቲካ የብቃት መለኪያ ነው …

የፖለቲካ ድርጅት እራስህ ሃሳብ አፍልቅህ በምትከውነው የተግባር ማሳ ውጤት እንጂ በሰው ሃስብ ተጠልልህ ዕድሜህን ሙሉ ለተከታታይ ዓመታት በተካሄደ ጽኑ ተጋድሎ ተጽዕኖ የፈጠረውን ነገር ሁሉ ጅራት ተከትለህ ከሆነ የትም አትደርስም። ያው እንደ ተለመደው ማህል መንገድ መቅረት ነው እንደታዬው፤ በታዬው መልክ መጠናቀቀ።


እኔ የሚገርመኝ ሰማያዊን ተጥልለው ያሉ ነፍሶች እንዲህ ዓይነት የአማራ የተጋደሎ ነፍስ ሲዘረፍ አብረው ለመዝለቅ ማሳባቸው ነው።

ለስንት ዘመን ይሆን ራስህ ባልደከምክበት ሁኔታ፤ ሰው ባደራጀው እዬተንጠለጠልክ ሥምህን አዬር ላይ በስጋት ወጥረህ፤ በመሸማቀቅ የምትቀቅለው። … ይሉኝታ የሚባል መቼም አልተፈጠረም … ሰው ምን ይለናልም የለም … አቻ ሊሂቃኑ ምን ይታዘቡም ታስቦ አያውቅም።



ነገም ሌላ ተጽዕኖ የሚፈጥር ሰው ተቋም ክስስተ ይገኝ በቃ ግልብጥ ብለህ ወደ ዛ ነው። አዝናለሁኝ በጣም። ለነገሩ የኦጋዴው ነፃ አውጪ ጋር የነበረው ከቶ አድርሻው የት ተደረሰ ይሆን? በቃ የሰሞናት የአዬር ላይ ተስፋን በትነህ ሰብሳቢ አልቦ ሽልክ ... ወይ እነ ሹልከት አሁን ደግሞ የብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ ክብር አስመላሽ አውራ ሁነኛ ... 
  • ·       ዘመን ያለሻረው መላቢስ ትልም።

 „የድምጻችን ይሰማ“ ጊዜ የነበረው ሸር ጉድም ይሄው ነበር። ያን ያህል ረጅም ሪፖርት የተደመጠበት። አርበኛ አትሌት ሊሊሳ ፈይሳም የዓለም አምደኛ ሆኖ ሲመጣ የነበረው ሽር ጉድ „ሊሊሳን ያላችሁ እስኪ እንያቸሁም ነበር“ እስከ አውሮፓ ህብረት ድርስ ለስብሰባ ያሰስጋበዘው ይሄው ነበር … ባይሆን እነሱስ ተከብረው ነው።

የአማራ የልቤዎች!

አማራ ላይ ሲሆን ግን ሙልጭ ያለ የተለመደ ዘረፋ ነው በቃ። እንዲያውም ይህን የህዝብ ድምጽ ያደመጠው ብአዴን ነው። ለዚህ ክብርም ሞገስም የሚገባው … የህዝቡን ፍላጎት በሆደ ሰፊነት ያስተናገደው፤ ህዝቡን ሳያበሳጭ በጥሞና እና በትዕግስት የያዘው።

ብአዴን የ አማራ ህዝብ ብሄራዊ ሰንደቁ ያለውን ቁርጠኛ አቋም በሚመለከት ለሚነሳለት ጥያቄ ሁሉ በብልህነት መልስ እዬሰጠ ራሱን ነው የማገደው። ማለት ለሚቀርቡለት ጥያቄዎች አስደማሚ መልስ ነው የሚሰጠው። በብሄራዊ ሰንደቁ ላይ ያለው ሙሉ ስብዕና የልብ ያህል ነው፤ ህዝብ የፈለገውን ማድመጥም ታላቅ ጸጋ ነው። እኛ የአማራ ተጋደሎ ላይ እባካችሁ ተው እያል ለምነን ነበር ይሄው … አሞራው በረረ ቅሉ ተሰበረ ሆነ ተሆነ ... አሁን ደግሞ ሌላ መሰላል ተፈለገ ... ታቅዳ የተከወነችውም ጉዳይ ነበረች። "ልብ ያለው ሸብ!"

  • ·       ጋድሎው በሠራው፤ ባሰበለው የተግባር ማሳ ላይ አለን ከማለት     

አሁን ከልካይ የለም መሬት ላይ ስንት ሥራ በሚሠራበት ወቅት በአለቀና ስንት ግብር በተከፈለበት የአማራ ታገድሎ የህውልውና ልቅናዊ የዓርማ ፈቃድ ላይ መለጠፍ።

በቃ የዛንም የዚህንም ዘራፍህ አንተ ራስህን ቆልለህ ተደራዳሪ እና አደራዳሪ … ዛሬ እኮ አማራ ታሪኩን የሚዘግበለት ተጠዋሪ አይደለም። እሳት የላሱ የአማራ ልጆች አሉለት …



የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ 27 ዓመት ሙሉ በሥነ - ልቦናው፤ በመንፈሱ፤ በትውፊቱ፤ በማንነቱ ዘራፊን አንቅሮ ተፍቶ ነው በቃን ያለው። አንይህ አንስማህ ያለው። አሁን ደግሞ በአዲስ ካፖርት እንዲህ ታምሱትአላችሁ … እየጣዳችሁ ሾልካችሁ ለበላህሰብ ስንቅ ሲቀርብ አንደ ተኖረ እኮ ብልሁ ህዝብ እሰተርጓሚ አያስፈልገውም። ያውቀዋል።

      የተጋድሎው ባነሮች የተሰሩት በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ነበሩ። 

እንዲያውም ከሰማያዊ በፊት እኔ አብይ ሆይ! በሚለው አቤቱታዬ ያቀረብኩት አንዱ ይሄውን ነበር። እንግዲህ ያን ጊዜ ሰማያዊ ፓርቲ ቫልዬም ወሰዶ ተኝቶ ነበር። ወይ ከፖርቹጋል አደራዳሪ እዬጠበቀ ነበር „… 
ክብረቶቼ ቅኖቹ የ አውነት ደፋሮች ወገኖቼ ...

አብይ ሆይ!በሚለው ዓውራ እርስ ኢትዮጵያዊነት እና ኦህዴድ ከሚለው ንዑስ ዕርአስ ላይ ጥያቄን አቅርቤያለሁኝ። አቤቱታው ከነሙግቱ እና ከእነ ማብራሪያው ስለሰራሁት ረዘም ያለ ነው። እንዲቀላችሁ ብዬ ነው ንዑስ እርእሱን የሰጠኋችሁ። 
ሰኔ 01.06.2018 ነው አቤቱታየን አቀርብኩት። 

https://sergute.blogspot.com/2018/06/blog-post_19.html“
ለጠ/ ሚር አብይ አህመድ አቤቱታ። አብይ ሆይ!

  • ·       ኢትዮጵያ ህዝብ የአማራ ተጋድሎን መንፈስ በዝምታው አጽድቆታል የአብዩ ድጋፍ ህብረ ቀለማቱ በዚህው ደመቀ።

አሁን በዬከተሞች የተካሄዱት ሰልፎች የአማራ ተጋደሎን የህልውና መሰረት መንፈስ ድምጽ ይዞ ሲመጣ በአቋራጫ እኔ ነኝ ያስፈጸምኩት ባይ ነው ውስጠ ወይራው ሰማያዊ ፓርቲ።

… ለነገሩ እነ ዶር ገዱ አንዳርጋቸውም፤ እነ አቶ ንጉሡ ጥላሁንም፤ ራሱ አቶ ተክሌም የሻው እዛው ስላሉ ህዝቡም መስካሪውም እዛው ስላለ ዕውነቱን አበጥሮ፤ አንተርትሮ፤ ስንዴ ከእንክርዳድ ይለየዋል። ባላቀ ውሳኔ ገብተህ አፈ ጉአባኤ እኔ ነኝ¡ አንዲትም ስለዚህ ሰንደቅ ዓላማ ግብር ያልከፈለው አቤቱ ሰማያዊ በውነቱ ሊያፍር ይገባል!ከ አማራ ተጋድሎ ጋር ውድድር ላይ መሆኑን አሳምረን እናውቃለን። አሁን የአማራ ወጣት ፍንክች የሚል አይደለም፤፡ 
  • ቧልት አቅም አይሆንም! 

ስንት ጊዜ ተወደቅ? አቅምማ ከዬት መጥቶ ካለተፈጥሮ፤ በቧልት አገር አልተገነባም። አገር የሚሠራው በላቀ የሃሰብ ፈጣራ እና ወገብን ጠበቅ አድርገው በታጠቁ ታታሪ መሪዎች ነው። አሁን ያለው የጠ/ ሚር አብይ ካቢኔ በትጋት፤ 7 ቀን ከሌት ካለ እረፍት በማበተል ነው። ውጤቱም እዬታዬ ነው። 


በ100 ቀን የስንት ዓመታት ጉቶ ትብትብ ጉዳዮች ነው የተከወኑት? ሃሳብ ላላቸው፤ ነግረዋችሁዋል እኮ ባለቅኔው ጠ/ ሚር „ሃሳብ የሌለው መሪ መሪ ሳይሆን ነጂ ነው“ ብለዋችኋዋል።

                     ዛሬ!

ውዶቼ ... እነዚህ የቀደሙ የታገድሎ መንፈሶች ከ አሁኖቹ ጋር ድል ማማ ላይ እንዲህ ይገኛሉ። በሌላም ሁኔታ ተቀናብረው ይሰራሉ። ታሪክ ለዘራፊዎች መሸለም ስለማይገባ። ትውፊት የጨርቅ ቦንዳ ስላልሆነ። ትውፊቱም ታሪኩም ለባለተሪኩ ሆኖ እንዲዘልቅ ይሰራበታል። ለዚህም ነው ዛሬ የተወሰኑትን ፎተዎች አደባባይ የወጡት!


ለማመሳካሪያ። ታሪክን ለቀመኞች ልንፈቅድላቸው አይገባም። 
ቢያንስ ሞጋች ሃሳቦችን በመረጃ እያቀረብን ልንፈትናቸው ይገባል። 
   


የመንፈስ ዘራፊዎችን ፈጣሪያችን ወደ ልቦናቸው ይመልስልን። አሜን!

የኔወቹ ኑሩልኝ።
ማለፊያ ጊዜ!

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።