ልጥፎች

ቢያንስ በሚያስደነግጠው

  እንዴት አደራችሁልኝ? ቢያንስ በሚያስደነግጠው የሰው ልጅ ድንገተኛ ችግር መደንገጥ እንዴት ቸገረን? እኛ ብቻ አይደለነም ዓለማችንም። ለዚህ ነው እኔ ክፋትን፤ ጭካኔን የሚመክት የፍቅር ተፈጥሮ ካሪክለም ይነደፍለት የምለው። ሰውና ሰው ምን እና ምን እዬተኳኳኑ ይሆን? ሥርጉትሻ 2024/05/21

አሽዋማ ልብ ሰንቆ

 አሽዋማ ልብ ሰንቆ ብሩህ ትውልድን ማሰብ አይቻልም። ሥርጉትሻ 2024/05/21

ማድመጥ እያራደ ዴሞክራሲ

  ማድመጥ እያራደ ዴሞክራሲ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ህልም ነው። አድማጭ ፖለቲከኛ አለን??? ሥርጉትሻ 2024/05/21

ዕውን የኢትዮጵያ የመንግሥት አደረጃጀት #ፌድራሊዝም ነውን?

ምስል
  ዕውን የኢትዮጵያ የመንግሥት አደረጃጀት #ፌድራሊዝም ነውን? የት ቦታ ይሆን አማራ በቁጥሩ ልክ ውክልና ያለው። በራሱ በክልሉም ሆነ ከክልሉ ውጪ። ይህ የፋኖ #መቅድመ የመደራደሪያ አንኳር ነጥብ ሊሆን ይገባል። የፖለቲካ ውክልና #ይሉኝታ ሊገዛው አይገባም። ፈጽሞ። "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል ሰው ግን አያስተውለውም።" የአማራ ህዝብ ደግነቱ፤ ችግርን ተሸክሞ መኖሩ መቀጫ እንጂ መመስገኛ፤ መከበሪያ አልሆነው። አሁን ያለው ሥርዓት ለዚህ የበቃው እኮ በአማራ ድምጽ ነው። ሌሎች የተከደኑ ጥረቶች ተዘሎ። ዕውነት ለመናገር አማራ እጁ አመድ አፋሽ ነው። ምንም ያልተደረገላቸው ጋዜጠኛ አቶ ታዲዮስ እና ወጣቱ ባለቅኔ በላይ በቀለ ለአብነት አሉ እንጂ።   ለእኔ ፌድራላዊት ኢትዮጵያ አይደለም። የፌዳሪዝልም ዕውነት ያለው አማራ ክልል ብቻ ነው። የቀደመው የመለሲዝም ክልሎች፤ የዛሬ የአብይዝም ተጨማሪ ክልሎች የፌድራሊዝም ጭላንጭል የለባቸውም። ድቅድቅ ጨለማ ናቸው። ገና ፊደል ያልቆጠሩ ልሙጥ። ልግጫ ነው። ደቡብ በጆግራፊ ነው የተደራጀው። ሌላው ደግሞ በተጫኝ #ዞጎች ። ዕውነቱ ይህ ነው።   አማራ ክልል አርጎባ፤ አገው፤ ኦሮሞ፤ ቅማንት ልዩ ወረዳ፤ ልዩ ዞን አላቸው። በራሳቸው የእኔ በሚሉትም አካል ይተዳደራሉ። የሚገርመው የፖለቲካ ሥልጣን ውክልናው ዞጋቸው ሌላ ሆኖ ኮታው ግን እንደ #አማራ ይወሰዳል። የነበሩት የአገር መሪወች ሁሉ ውህድ ማንነት የነበራቸው፤ ወጥም የሆኑት አጤ የኋንስን ሳይቀር አማራ የሚከሰሰው እሳቸውም አማራ እንደሆኑ ነው።   ኮነሬል መንግሥቱ ኃይለማርያም ኦሮሞ ናቸው ነው የሚባለው። አጤ ኃይለሥላሴም ቅንጣቢ የላቸውም ከአማራ ነው የሚባለው፤ ግን የአማራ ገዢ መደብ ይባላል። አጤ ሚኒሊክም ውህድ ማንነት የነበራቸው ናቸው።

መኖር ቀለበት ነው።

  መኖር ቀለበት ነው። ቸር እደሩልኝ። አሜን። ሥርጉትሻ 2024/05/2024

መስዋዕትነትን ማመጣጠን፦ መቀነስ በትግል ዓለም ውስጥ ሊታቀድ የሚገባው በኽረ ጉዳይ ነው።

  መስዋዕትነትን ማመጣጠን፦  መቀነስ በትግል ዓለም ውስጥ  ሊታቀድ የሚገባው በኽረ ጉዳይ ነው።   እንዴት ናችሁ የአገሬ ልጆች።   ደህና ናችሁ ወይ። በለውጥ ጊዜ የሚሆን ነው እዬተባል የትውልድ አጨዳ እና ጉስቁልና፤፦የኢኮኖሚ ድቀት እና እንግልት እንደ ጀብዱ ባይታይ ጥሩ ነው። ትግል ላይ ያለውም ቢሆን ትርፍ እና ኪሳራውን መዝኖ አትራፊነት ሚዛን እንዲፋ ጥበብን ማከል ይገባል። ሌላው አቅም የለሹም አቅም እንደሌለው አምኖ በፈቃዱ በሚችልበት መሳተፍ ብልህነት ነው። ምክንያቱም አዳዲስ ተቋም ተፈጥሮ ለስኬት ሳይበቃ ሲተን በዛ ውስጥ የፈሰው አቅምና የተገበረው ህይወት እውቅና ሊሰጠው ይገባል። በተጨማሪም ተደጋጋሚ ግድፈት እንዳይኖር ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል። አትራፊነት ከአመራራ አቅም ተመክሮ ይመነጫልና። የሆነ ሆኖ ለትግል፤ ለስኬት፤ ለሂደት እንደሚታሰበው ሁሉ ያ 50 ዓመት ሁሉ እንደ ጥንቸል ሙከራ የሚደረግበት ህዝብ መስዋዕትነቱ በቀነሰ መልኩ እንዲሆን ሊታሰብበት ይገባል።    በዚህ የ50 ዓመት ተጋድሎ ድልን በመቋደስ ብቻ ተጠቃሚው ደቡብ ነው። መልካም ነው። ግን ይህም ሊጠና ይገባል። እንደ አንድ ፕሮጀክት ምርምር ሊካሄድበት ይገባል። የትውልድ ጉዳይ የሚያገባው ሁሉ ይሰብበት። የደቡብ ብልህነት ጠቀሜታው ይጠና። በጥሞና። ማገዶነትም እስከመቼ ሊሉ ይገባቸዋል የተማገደውን የሚማገደውን ማህበረሰብ እንመራለን የሚሉ ወገኖቻችን። ለምሳሌ ኢዲዩ፤ ኢህአፓ፤ ሻብያ፤ ከፋኝ፤ ግንቦት 7 // እራሱ ኦህዴድ የትግል በዓቱ ስሜን ነው። ስሜነኞች ከትምህርት ተገልለው ሲታገሉ አቶ ኃይለማርያም ደስአለኝ ይማሩ ነበር። በኋላ የጠሚ ቦታ ለአቶ ገዱ፦ ወይንም ለዶር አንባቸው አልተሰጠም አቶ ደሳለኝ ኃይለማሪያም ጠሚር ሆኑ፤ በጦርነቱ ስንት ስማርት እንደወጣ ቀርቷል። የስሜን ህዝቡም ነበ

#ህም! #ህም። #ህም።

  #ህም ! #ህም ። #ህም ። "ገዢው የዞግ ድርጅት ተፎካካሪወችን፤ ተቃማዊወችን ማፈን መብቱ ነው። ሥራውም ነው እንደ ድከመት ሊታይ አይገባም" የሚል የአማራ ሊቅ ለዛውም የህግ አንበል? ምጥ ነው። እንዲህ ከተባለ #ዴሞክራቶች #ሪፓብሊካን ይፈኑን? #ያሳድዱን ? #ይገቱን ? የሚገርመኝ አወያዩም አልሞገተም። አንድ ሚዲያ ላይ ክፍል ሁለት ውይይት ላይ ነው ያዳመጥኩት። አወያዩም እንደ ቅዱስ ቁርባን ተመስጌን ብሎ የተቀበለው ይመስላል። የማይሰማ የለም። ውዶቼ ደህና ቆዩኝ። ሥርጉትሻ 2024/05/2024

ኧረ ተው አቤ ቱክቻው #ፋኖ #ተብዬው ትላለህን?

ምስል
  ኧረ ተው አቤ ቱክቻው #ፋኖ #ተብዬው ትላለህን?    የናቁት ይወርሳል እንዳይሆም። የዕለት አጀንዳችሁ #ፋኖ ነው። ገቢያችሁም። ደግሞም #መንፈሱን #ትፈሩታሳችሁ ። ለዚህም ነው ለሚዲያችሁ #ጉልላት አጀንዳ የሆነው። ማጣጣል፤ ማቃለል፤ አሳንሶ ማዬት አይገባም። ህዝባዊ ንቅናቄም ነው። ኢትዮጵያን ትወዳለህ የፋኖ ትጉኃንን፤ ፋኖን በመንፈስ የሚደግፋ ሳይለንት ማጆሪቲው እኮ የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው። ፋኖ፥ መነሻ መሠረቱን አባዬ ገበሬውን ንቀህ ይሆናልን???? "ጽንፈኛውም" ትላለህ። መንፈሱ ላይ ብታተኩር ይበጅ ይመስለኛል። ፋኖ መንፈሱ ንፁህ ነውና። የሚመራውም እኔ የማውቀው በጎበዝ አለቃ ነው። ተፈጥሯዊም ነው። ቢሮክራት፤ የፖለቲካ ድርጅት የፖሊት ቢሮ የለለው። ከዚህ ተፈጥሮው ከወጣ አደጋው ሰፊ ነው። ኢትዮጵያ ካለተፍጥሯዋ ሶሻሊዝምን ተሸከሚ ተብላ ነው እንዲህ ብትልትል የምትለው።   የሆነ ሆኖ በፋኖ ላይ አሉታዊ ሁኔታወችን ጠርቀምቀም አድርገህ በዛ ላይ ትጋትህ መብትኽ ቢሆንም ህዝባዊ ንቅናቄን አጣጥሎ ማዬት አይገባም። ለውጥ ተብዬው መነሻውም የአርበኛ ጎቤ መንፈስ፤ መዳኛውም በህወሃት ሲጠቃ ትንታጉ ፋኖ በአባት አደሩ ይተብኃል እንደመከተ ልብህ ያውቃዋል። ህወሃቶችም እንደሚፈሩት ታውቃለህ። ቢያንስ ሰማዕታቱን እንዴት ማክበር ተሳነህ? #የአብይዝም #ፋኖወችም #አሉልህ እኮ። አንድ ሰሞን ብቅ ብለው የተነኑ። ግን በስል ገብተው የሚያተራምሱ። መረጃ እዬሰጡ የሚያስመነጡሩ። የራሳቸውን ወንድሞች የሚያስጨርሱ። #እጅ #ሰጡ የሚባሉት እነሱ ናቸው። እንዲህ በወል ስታቃልላቸው ማዕዳችሁ አንድ ስለሆነ ከአብይዝም ፋኖወች ጋራ እንዳይከፋብህ። ሌላው ግን ፈጣሪ ያውቃል። እሱ ይዳኜው። እሱ ይጨመርበት። ነገም አብሮ መሥራት ሊኖር ይችላል። ማቃለል ለ

"ምርጫ ጠብቁ፤ በቀጣዩ ምርጫ ተወዳደሩ።"

ምስል
  "ምርጫ ጠብቁ፤ በቀጣዩ ምርጫ ተወዳደሩ።" "ወዮ ወዮልሽ ይላል ጌታ እግዚአብሄር ከክፋትሽ ሁሉ በሗላ የምንዝርናን ሥፍራ በዬአደባባዩ ከፍ ያለን ቦታ ሠራሽ።" (ትንቢተ ህዝቃዬል ምዕራፍ ፲፮ ቁጥር ፲፪)   ይህ ልግጫ ይመስለኛ። እርግጫም። ምርጫ አልተካሄደም እያልኩ አይደለም። ምርጫው እንደምን ተፈፀመ ነው ጉዳዬ። አስር ዙር ምርጫ ቢካሄድ በጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ዘመን ምርጫን ተወዳድሮ ማሸነፍ ይቻላል ብሎ ማሰብ ፀሐይ ጨረቃን ትተካለች እንደማለት ነው።   ይህን ጉዳይ በወቅቱ ዓለም ዓቀፍ ሚዲያ በአውንታዊነት ሲገልፁት፤ ዬኛም ሰወች በሰላም ተጠናቀቀ ሲሉ ጽፌበት ነበር። አሁን በአማርኛ ቋንቋ አብራርቼ ልፃፈው። በተለይ አቶ ወንድም አቤ ቱኩቻው አዘውትሮ ስለሚገልፀው።   ከምርጫ በፊት ምን ተከናወነ?   1) የተፎካካሪ ኃይሎችን ከውጭ ወደ አገር ውስጥ ሲያስገቡ ጫጉላ ቤት አስገቧቸው። እስከ እንግዶቻቸውድረስ ሆቴል ተከራይተው ቅብጥ እና ቅልጥ አደረጓቸው። ቀልባቸው የወደደውን አጠጋጉት። ጠንካሮችም ዛሉ። መስተንግዶው በዛ። የእኛአገር ሰው ደግሞ ይሉኝተኛ ነው። አልፎ አልፎም አምስትም አስርም አባል የያዙትን በሥም እዬጠሩ ማቆለማመጥ ተያያዙት። እና የሰባዕዊ መብት ተሟጋች የነበረው፦ አራት ዓይናማው ጋዜጠኛ፦ ሞጋች ፀሐፍት፤ የጥበብ ሰው ከውጭ ወደ አገር የገባ ሁሉ በዓይኔ ሂድ ተባሉ። ያ ትልቁ መደላድል ነበር። 2) በሰላም ሚኒስተር መቋቋም እና ሂደቱ በራሱ ለኖቤል እጮኝነት ዓውድ ነበር። ለምርጫም ጥርጊያ መንገድ። 3) ለአንድ ቀን ብቻ ሥራ ላይ የዋለ የተፎካካሪ ፓርቲ ሊቀመናብርትን፤ በህዝብ ተወዳጅ እና ተጽዕኖ ፈጣሪያትን በተለያዬ ኮሚሽን በማደራጀት ሹመት ተሰጠ። ማዘያ። 4) ተስፋ የተጣለባቸው የአማራ ክልል መሪወች ተፈጁ።

ዓለም ያልሞከረችው የአሉታዊ ዴሞግራፊ አዲስ ጥላሸት ምዕራፍ በኢትዮጵያ። #በትምህርት፤ #በዕውቀት፤ ዘርፍም።

ምስል
  ዓ ለም ያልሞከረችው የአሉታዊ ዴሞግራፊ አዲስ ጥላሸት ምዕራፍ በኢትዮጵያ። # በትምህርት ፤ # በዕውቀት ፤ ዘርፍም። " ኃጣን እንደ ሊባኖስ ዝግባም ለምልሞ አዬሁት። ብመለስም ግን አጣሁት፦ ፈለግሁት ቦታውንም አላገኜሁት። " ( መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፴፮ ቁ - ከ፴፭ ፴፮ )     አንድ የማህበረ ቅንነት አባልተኛ " አጀንዳ ማስቀዬሪያ ነው " ሲሉ ዕይታቸውን በቅንነት አጋሩኝ። አመሰግናቸዋለሁኝ። ትንሽ ግን ማብራራት ገለጥለጥ አድርጎ መፈተሽ ይገባል። ይህ ተራ ዜና አይደለም። መንፈስን አወላልቆ አምሳያውን የሚገጣጥም የመንፈስ ነቀላና ተከላ የገዳ ሥርዓት ሁነኛ የዘመነ አሉታዊ ዴሞግራፊ ነው። ገዳይ ትልም ነው። # ዴሞግራፊን እኔ በሁለት እከፍለዋለሁኝ። እንዲህ …… 1) አወንታዊ ዴሞግራፊ። 2) አሉታዊ ዴሞግራፊ። 1) አወንታዊውዴሞግራፊ በተፈጥሮ አደጋ፦ በመሬት ለምነት መበላት፤ በቦታ ጥበት ለኗሪወች ምቹ ሁኔታንለመፍጠር ይከወናል። ይህም ሲሆን በመንግሥት በጎ ፈቃድ ብቻ ሳይሆን ከነባር በዕቱ የሚነሳው ህዝብ ሲያምንበት ብቻ የሚከወን # ሰባዕዊነትም ነው ለእኔ። 2) አሉታዊ ዴሞግራፊ ነዋሪው ፈቃዱ ሳይጠዬቅ ተገዶ ሲለቅ። ወይንም እንደ ዶር አብይ መንግሥት የህዝብ ስብጥርን ለመበወዝ በጭቆና እና በመዋጥ ሲከወን ይሆናል። እንዲህ የሚያደርጉ ሥርዓቶች # የፋሺዝም # ቅኝቶች ናቸው። ለዚህም ነው እኔ በጥዋቱ አሉታዊ ዴሞግራፊ ሲከወን አቅጣጫው ፋሺዝም መሆኑን በመረዳት አቅምን በገፍ