በነገረ ሐራ መሬት የነገ #ስጋቴን ብገልጽስ? #ነገን ሰላማዊ ተከታይ ስለማድረግ።
በነገረ ሐራ መሬት የነገ #ስጋቴን ብገልጽስ? "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። #ምዕራፍ ፲፱። #ጠብታ ። በብልጽግና መንግሥት የተፈቀደለት ሽምቅ ተዋጊ ኃይል በአፋር እንዳለ ሳድምጥ ቆይቻለሁኝ። ለሽምቅ ኃይሉ የፖለቲካ ክንፍ እንደተደራጀለትም ይገባኝ ነበር። ግን የእኔን የመረዳት መጠን መሬት ላይ ካለው የራሱ አካል ማረጋገጫ እስኪሰጥበት ድረስ ጸጥ ብዬ መጠበቅ ነበረብኝ። ሰሞኑን በአርተስ የዜና ዕውጃ ከስምረት ፖለቲካል ፓርቲ በተገኜ መረጃ መሰረት የኃራው ታጣቂ ሸማቂ ኃይል ክንፋ እንደሆነ ዜናው ያትታል። እኔም አውቄው ስለነበር አላስደነገጠኝም። እንዲህ ገልፆ መናገር መልካም ነገር ነው። #ጥቃትን መቅደም እና መቀደም። በጣም ከሚያሳዝኑኝ የዓለም ማህበረሰብ ውስጥ ሊባኖናውያን አንዱ ናቸው። ሊባነን መንግሥት አላቸው። መንግሥታቸው ግን ለህልውናቸው ቀጣይነት የደህንነት ዋስትና የመስጠት አቅም የለውም። አቅሙ ያለው ከመንግሥት ውጭ የሆነው #ሂዝቦላ ነው። የሂዝቦላ የፖለቲካ ክንፍ የሊባኖስ ማዕከላዊ መንግሥት ሳይሆን አገረ #ኢራን ናት። የኢዝቦላ ተቋማት ሁሉ በሊባኖሳውያን ውስጥነት ታዳሚወች ናቸው። ወጩ የሚሸፈንለት በኢራን መንግሥት ነው። የሂዝቡላ የፖለቲካ ያው ሃይማኖታዊ ነው፤ የታጣቂ ኃይል መሪ የኢራን መንግሥት ፖለቲካ ነው። ሂዝቦላ ለሚወስደው እርምጃ ዋጋ የሚከፍለው ደግሞ መከረኛው የሊባኖስ ህዝብ ነው። ይህ ወጣ ገብ ሁነት የተፈጠረው ከጥንስሱ የሊባኖስ መንግስት የራሱን የፖለቲካ፤ የሚሊተሪ ሉዓላዊነት ማስጠበቅ ባለመቻሉ ነው። የዘገዬ እና ፍዝ አቋም ያለውም ነው። አሁን የሊባኖስ ንጹኃን የሚከፍሉት ዋጋ ተመን ሊወጣለት የማይችል ነው። ከሊባኖ...