ግን የት ደረሰ?
"ኑ አገራችሁን ግቡ።" ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ። "ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን።" ግን የት ደረሰ? "ቀን የሚያመጣውን ምን እንደሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።" (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፯ ቁጥር ፩) #ምዕራፍ ፲፱። "ኑ አገራችሁን ግቡ። #ስንኖር ኢትዮጵያዊ፤ #ስንሞት ኢትዮጵያ" በምልሰት የሚጠይቅ አገላለጽ ነው። ብለህ ነበር፤ ያልከው ሆኖን፤ ምን አሳካህ፤ ምንስ አጎደልክ የሚል የህሊና ሙግት ጋር እራስን #ያገጣጥማል ። ስንኙ - ያማልላል። ውስጥን - ይደላል። ግን ገቢር ላይ ተፈትኖ የወደቀ ጽንሰ ሐሳብ ነው። በውስጡ የሌለ ጭብጥ ዕውንነቱ ከመፈጠሩ በፊት #ክስመቱን ስለሚያውጅ። ቀድሞ ነገር ኢትዮጵያ #የማን ናት? ኢትዮጵያን #የሚያዝባትስ ማነው? ለኢትዮጵያዊነት ዜግነት ሰጩ፤ #ነሹስ ማን ነው? #ኢትዮጵያዊነት በገብያ ንግድስ ይተዳደራልን? የገዘፋ ጥያቄወችን በዚህ ዙሪያ በብዙ ማንሳት ይቻላል። መላሽ ካገኙ። እንደ እኔ እምነት ኢትዮጵያዊነት በገብያ ህግ ሊተደደር አይችልም። ኢትዮጵያም የኢትዮጵውያን ናት። ኢትዮጵያን የሚያዛት፤ መታዘዝ ካለባት ህዝቧ ብቻ እንጂ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ወይንም፤ አንድ ዞግ ሊሆን አይችልም። ለኢትዮጵያ ዜግነት ሰጩም ነሹም፤ ውጡ ግቡም ብሎ የመበየን የአንድ የፖለቲካ ድርጅት መሪ ሥልጣን በፍጹም አይደለም። ሊሆንም አይችልም። በማንነት ጉዳይ የሚሰጠው ብይን የግንዛቤ እጥረት ወይንም አቃሎ የማየት፤ ወይንም የውስጥ ቀውስን ለማስታገስ ካልሆነ በስተቀር የማንነት ጉዳይ አገር፤ አህጉር፤ ሉላዊ በሆነ መንፈስ ስናዬው ለሰው ልጅ የተሰጠው የነፃነት መንበር፣ ላዕላይ የሆነ የክብሩ መገለጫ፣...