#ሌላው …
#ከእናት ይሆን የተፈጠሩትን? "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ። " አሜን። #ምዕራፍ ፲፰ የአንድ ከተማ ህዝብ #ምጥጥ ያደረገውን አረመኒያዊነት ከሴቶች በላይ ማን ግንባር ቀደም ተሟጋች ይሁን? በዘመነ ህወሃት እታገልበት የነበረው ሞቶ የኢትዮጵያ ሴት የፖለቲካ ሊቃናት ከፖለቲካ ሥልጣን ስለተገለሉ የኢትዮጵያ እናቶች ዕንባ አባሽ አጡ። የኢትዮጵያ ፖለቲካ የገበርዲን እና የከረባት ያደረገው ሁነት ሊቀየር ይገባል ነበር ሙግቱ። ይህም ተቀባይነት ብቻ ሳይሆን የህወሃትን መንበረ - ሥልጣን የነቀለ ጉልበታም አመክንዮ ነበር። ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድም 50% ካቢኔያቸው በሴት ሊቃናት የሆነው የዛን ጊዜ ከወንዝ ዳር የታፈሰ ዝቀሽ ጉዳይ ሆኖ አልነበረም። ለስልጣነ - መንግሥታቸው የዲፕሎማሲ ማህበረሰቡን ቅቡልነት፤ ቀልብ በመሳብ የዓለም ተጽዔኖ ፈጣሪ ፖለቲከኞች የተረጋጋ #ታማኛዊ መንፈስ እንዲቀልቧቸው አስበው የፈጸሙት ጉዳይ ነበር። ከለወጡ ከሚፈለጉ መሰረታዊ ጉዳዮች የሴት ፖለቲከኞች ዕውቅና እና የፖለቲካ #ውክልና በእጅጉ ያስፈልግ ነበር። ዕውነት ለመናገር አሁን እንዲህ ዓይነት ሙግት አላነሳም። ከላይ እስከ ታች በሴት የፖለቲካ ሊቃናት ተሞልቷል። ነገር ግን አንድም ሊቅ #እናትነታዊ ጥሪው አነሳስቶት ከቅርባቸው ያለውን የደብረብርሃን #የተፈናቃይ ማዕከል ሄደው አይተው አያውቅም። በሌሎችም የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ላይ ምንም ዓይነት ሰዋዊ፤ ተፈጥሯዊ ድርጊት ላይ ሲገኙ አላስተውልም። አቤቱታ ሳቀርብም አያዳምጡኝም። ትንሽ ዶክተር ሊያ ታደሰ የቀድሞዋ የጤና ሚር ያዳምጡ ነበር። እኔ ቀን ከሌት "አብይ፤ አብይ" እያልኩ አልባንንም። ካቢኔ አለ። ህግ አውጪ፤ ህግ ተርጓሚ ...