#ይሁንታ

 

የህዝብን #መታመን #የሚደፋ የአገር መሪ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ #ሰላማዊነትም የሚረብሻቸው ይመስለኛል። 
 
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
 
#ምዕራፍ ፲፯። ነገረ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ጠቅላዩን ህልማቸውን ያሳካ መንፈስ ያለበት ነው።
ጤና ይስጥልኝ የማከብራችሁ የአገሬ ልጆች? እንዴት አደራችሁ ዋላችሁ?
 
ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊን #አሳቻ መሪ ናቸው ማለቴ ከትናንት በበለጠ ዛሬ ትርጉሙ እየበራ ነው። በደርግ ዘመን ቅኔው ጎጃም #የሰላም በዓት ነበር። በጠቅላይ ሚር አብይ ዘመን ህወሃት አቅዶ ሰቆቃ ያልፈጸመበት በዓት #ጎጃም ነበር። እንደ ማዕከላዊ ጎንደር፤ እንደ ሰሜን ተራራም ሴራ ህወሃት አላደራጀበትም። 
 
ምንም ዓይነት የህወሃት በቀል በሁመራ ከተማ አልተፈጸመበትም። ተመስጌን ብዬ ብዙ ጽፌበታለሁኝ። ጠለምት፤ አዳርቃይ፤ አዲረመጥ፤ ማይጠምሪ እንዲሁም ራያ እንደ ጥንቸል የሰቆቃ መሞከሪያ ጣቢያ ናቸው። የሆነ ሆኖ ቀለሜዋ ጎጄ ዛሬ ግን ከጎንደር ሰቲት ሁመራን ሳይጨምር፤ ከወሎ እና ከሽው ጋር የሰላሙ መታወክ ሁነት በቅኔው ጎጃምም #እኩል ሆኗል። ስንት ፈላስፋ፤ ስንት ሳይንቲስት ሊያፈራ የሚችል ባለተሰጥዖ በዓት ነው ጎጄ።።።።።።
 
ከዚህ ሃሳብ ስነሳ የሰቲት ሁመራ የወልቃይት እና ጠገዴ ዞን ብቸኛው በአማራ ክልል ካሉ ዞኖች #ፍጹም ሰላም የሰፈነበት፤ ለኢትዮጵያ ሠራዊት #ቅንነቱን በአክብሮት የሚመግብ ብቻ ሳይሆን፤ የአገር መከላከያውን #የእኛ ሠራዊት ብሎ ደፍሮ የሚናገር፤ በየትኛውም የፋኖ ንቅናቄ ቁጥብ የሆነ፤ #ነፍሱን አድምጦ፤ ከችግር - ተምሮ፤ #ማስተዋልን ውጦ ሁሉንም ዓይነት የፈተና ወጀብ ችሎ በጸጥታ፤ በእርጋታ ያለ ህዝብ የወልቃይት እና የጠገዴ ህዝብ ነው።
 
ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድንም #መሪያችን ነው የሚሉት። ሃይማኖታቸውን የቀየሩም ውጭ የሚኖሩ አሉ። ብልጽግና ህዝብ አለኝ ብሎ እንደ #በሻሻ 100% መናገር የሚችለው #ወልቃይት እና ጠገዴ ብቻ ነው ማለት እችላለሁኝ። 
 
ሲጀመር ለጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ የተሰጠው ሙሉ ፍቅር እና አክብሮት #ያልጓጎለው#ያልተስተጓጎለው#ያላጎፈረው#ጎሽቶ ያልጎረፈበት ባድማ ቢኖር ይኽው ዞን የሰቲት ነው። አመራሮቹም ውስጣዊ የሆነ የመጽናት አቅማቸው አንቱ ነው። አቅልም፤ አደብም የሰጣቸው ናቸው። በጀት - ቢታገዱ፤ ፊት ቢነሱ፤ አዲስ አበባ ሄደው ጠቅላዩን ለማግኜት ጥረት አድርገው ሳይሳካ ቢቀር፤ በብልጽግና ካቢኔ አንኳሩ #አንባሳደር ሬድዋን ሁሴን ያላቸውን የአተያይ፤ ዝበት ያለው ዕይታ እና #ንቀት። በትዕግሥት ታልፏል። እኔም እራሴ ዝም ብዬ ነው ያዳመጥኩት። እሳቸው ለዚህ ጉዳይ አናት ናቸው። ከውስጣቸው ጎንደርን ማግለላቸውም #አመክንዮዊ ነው። 
 
አንባሳደር ሬድዋን ሁሴን ጎንደርን መበቀል ይፈልጋሉ። ለዚህ የዕድል #ተሃድሶ የተገኜው ግን በጎንደር መንፈስ ስለመሆኑ ተሰውሮባቸዋል። ብዙ በጣም ብዙ ተደክሞበት ነበር የህወሃት መንበረ ስልጣን እንዲያከትም። የዛ ድል ድጋሚ ተጠቃሚ እሳቸው ሆነዋል። ዕድሉን ሌላ ወስዶት ቢሆን የህወሃታውያን የሠርግ እና መልስ ግጥግጥ ተኖ በቀረ። 
 
የሆነ ሆኖ ለፍቅር ተፈጥሮ ግድ የማይሰጣቸው ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ከግድፈታቸው አይማሩም። ሰሞኑን ጨካኙ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ያወጣው በምርጫ ሰሌዳ #ይሁንታ በተባበሩት የአፍቅሮተ ህወሃት ይሁንታ ነው ብዬ አምናለሁኝ። ፍቅርበፍቅር ለምን? ስለምን? አብራርቼ በቀጣይ እጽፍበታለሁኝ።
 
የሆነ ሆኖ ወልቃይት ጠገድቸወች እንደዚህ ዘመን ሰላም ጋር ተዋውቀን አናውቅም እድሜ ለዶር አብይ አህመድ ቃለ #ምህዳናቸው ነው። መሬት ላይ ያሉት ብቻ ሳይሆን ውጭ አገር ያሉ እኔ እማገኛቸው። በአንድም በሌላም እኔ እጠይቃቸዋለሁኝ። ውጭ አገር ያሉትን። ቤተሰቦቼም ናቸው። የእኔም የህሊናዬ ጉዳይ ስለሆነ ሳዋጣቸው የሚገርም መልስ ይሰጡኛል። በጣም በዶር አብይ አህመድ ይተማመናሉ። ለእነሱ ብልጽግና #ትርታቸው ነው። ጥቅሙን የሚፃረር ተጠቃሚ ስለለ። 
 
የሆነ ሆኖ ጸጥ ብሎ፤ ውስጡን ለሰጣችው የሰቲት ሁመራ የወልቃይት፤ የጠገዴ ዞን ህዝብ የመታመን አቅማችውን የሚለኩበት አጋጣሚ ይሆንላቸዋል ብዬ አስባለሁኝ ለሰው ልጅ መብት ብጣቂ ክብር የሌለው፤ #ባለወለደ አንጀቱ ጭካኔውን ያሳዬን ምርጫ ቦርድ ድፍረቱም ቢገርመኝም፤ #ቀጥል የሚል መመሪያ ካለቃው ከዶር አብይ አህመድ አይሰጠውም የሚል ዕምነት የለኝም። የህዝቡን የልብ ሽፍትነት፤ እልቂት ናፋቂ እርምጃ ነው። ጸጥታው መረጋጋቱም ተቀንቶበታል።። 
 
የሰላም ሚ/ ር ያቋቋሙት ጠቅላይ ሚር፤ የዓለሙ የሰላም አባት ሎሬት ሆነው የኖቤል ተሸላሚ የሆኑት ጠቅላይ ሚር ሰላማዊ የህዝብ አስተዳደር እና ቅንነትን የሚሹት መይመስለኝም። አዲስ - ብጥበጣ፤ አዲስ ገጭ ገው ይናፈቃቸዋል። አሁን ህወሃት በአራቱም መዕዘን ጦርነት ከፍቶ እንደ ገና የእልቂት፤ የድቀት መታሞ እያደለቀ የጨካኙ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ማከያ ቤንዚን ታቅዶ የሚከወን የፖለቲካ ትራጀዲ ነው።
 
ማህበረ ኢህአዴጋውያወህወሃትውያን የደቡብ አፍሪካን ስምምነት አፍርሰው ሲገባበዙ፤ ሲሸላለሙ፤ ሲሿሿሙ ባጁ። አሁን ደግሞ ማይካድራ ተረስቶ ህሊናን የሚጨፈላልቅ የንቀት እርምጃ ተወሰደ። የሚሰቀጥጥም የምርጫ ሰሌዳ ወጣ። "#ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ"
 
ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን።
ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።
ኑሩልኝ። አሜን።
ሥርጉተ©ሥላሴ
Serute©Selassie
2/2/2026
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።
ፍቅር ሲያልቅ ትዕግሥት ይሰደዳል።
ትዕግስት ሲያልቅም ፍቅር ይሰደዳል።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።