ትውልድን #ከሞገድ ላይ ካለው ምኞቱ አውርዶ በፋክት፤ በመርህ እንዲሞግት ብቃት ይሰጣል።

 እንዴት አደርን? ጉንፋን እንዴት ይለቅ ይሆን? 365 ቀናት እኔ እና ጉንፋን ጉልቻ ላይ? የሆነ ሆኖ "ዛሬ ዕለቱ" ሰከን ብሏል? ሸጋ ነው። ምን ልላችሁ ነበር? እ። ፕ/ ዶር ተሾመ አበበ በመረጃ የተደገፈ ሙያዊ መግለጫ አንከር ሚዲያ ላይ ሰጥተዋል። ማስታወሻ ተይዞ የሚማሩት ገለጣ ነው። ድክመታችን፤ ፈተናችን እንዲህ ሙያዊ ትንተና ሲያገኝ #ትውልድን #ከሞገድ ላይ ካለው ምኞቱ አውርዶ በፋክት፤ በመርህ እንዲሞግት ብቃት ይሰጣል። የሚደንቅ ነው ትጥቅ አስፈች ዕይታወችን ሁሉ በረጋ አቀራረብ ሞግተዋል። "በኢኮኖሚ ውድቀት ሥርዓት ይፈርሳል" የሚለውን ዕድምታ "ትጥቅ አስፈች" ብለውታል። ግን በከረረ አገላለጥ አይደለም። በእናታዊ አገላለጥ። በጣም ጠቃሚ መምህር የሆነ ገለጣ ነው። ከዚህ ቀደምም የሰጡት ሁሉ ሰኃ የማይወጣለት ነው። የልጅ መሳይ ብርቱ አቅሙ እሱ ልተንትነው፤ ልበትነው አይልም #አብዛኛውን #ጉዳይ ከባለሙያ ጋር ይወያያል። ይህቺን ሲያደርግ አያመልጠኝም አዳምጠዋለሁ። የቤተ እግዚአብሄር ከሆነም ለተሰጣቸው ዕድሉን ሰጥቶ ያወያያል። ማለፊያ ነው። ይፈቀድልኝ አይፈቀድልኝ ስለማላውቅ ሼር አላደረኩትም። ሄዳችሁ ግን እንድታዳምጡት በትሁት ብዕሬ አሳስባለሁ። ሥርጉትሻ2024/05/29

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።