ልቅና በልዕልና፨ ቢስ አይይብን፨ አሜን፨ #ማህበረ #ቅንነት እንዴት አደራችሁልኝ። ኑሩልኝ ክብረቶቼ።

#ማህበረ #ቅንነት እንዴት አደራችሁልኝ። ኑሩልኝ ክብረቶቼ።
ዛሬ እማመሰግናቸው ወጣቶች አሉኝ። የፀጋዬ ራዲዮም ለ16 ዓመት የተጋበት፤ የከበቡሽ ልሳንወርቅ ሚዲያም ከውስጡ፤ ከህሊናው ዝቀሽ ተስፋን ሰንቆ ያመሰግናቸዋል። ትናንት ሙሉው ቀን እስከ ማምሻ ድረስ ስለነሱ ነበርኩኝ። ይገባቸዋል። አዋርዳቸው ምስግና ነው። ሽልማታቸው ምርቃት፤ ፀሎት እና ድዋ። አልጠግባቸውም። እነ ማህበረ #ማንጠግቦህን
 
1) #ሩህሩሁ ኮሚዲያን እሸቱ መለሰ፤
2) የሙያ #ህግ አክባሪው ጋዜጠኛ ግዛቸው አሻግሬ። ምን የቀረው አለና በፍቅር እኮ እያስተዳደረን አይደል? " ልጅ ግዛቸው"
3) #የሳቁ አጤ አቶ ማንያዘዋል እሸቱ፤
4) ቡናዬን #ዝምን ያደረጋት ሊቀ - ትጉኃኑ አቶ ከናዕን አሰፋን፦
5) #የእሽታ አውታሩ አቶ ጥጋቡ ኃይሌ፦ የአወንታዊነት አርበኛዬ።
6) መሳጩ #ልዩ አቶ ኢዘዲን ካሜል። 
 
በተለይ ሚዲያ ላይ የሚሠሩት ለሚዲያ #ትርታ ናቸው። ሁሎችም ትህትናን ዕውቅና የሰጡ ወጣቶች ናቸው። ርህርህናን የተቀበሉ ወጣቶች ናቸው፨ ፈርኃ እግዚአብሄር፤ ፈርኃ አላህም ያላቸው፤ አምላካቸውንም ያስቀደሙ፤ #ለአላዛሯ ኢትዮጵያ የተስፋ #ብራወች ናቸው። #እስፔኖችን #ቢስ #አይይብኝ። አሜን።
 
 
 https://www.youtube.com/channel/UCJEQXw86u_NG4A1FVC1j2qg
መልካም ሰንበት።
መሸቢያ ውሎ አዳር።
ኑሩልኝ።
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
13/07/024
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።