#መጠሪያችን ማን ይሆን ዘንድ ከቶ ፈቀድን???? #ጦርነት እኮ #የሞት #ዓዋጅ እኮ ነው። ይህ በፍቅር እፍ ያደርገናል።
#መጠሪያችን ማን ይሆን ዘንድ ከቶ ፈቀድን????
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
#ምዕራፍ ፲፰
#ግን እኛ አድራሻችን ፍጥረተ ነገራችን ከያት ይሆን?
#ሊለምኑ ያፈሩ ሚሊዮን ወገን ያለን --- - እኛ
#ለአንድ ሰዓት እንኳን የሚያቆይ የለት ደራሽ የምግብ ክምችት የሌላቸው በሺህ የሚቆጠሩ ቤተሰብ ያለን --- - እኛ ---
#የሚሠሩ እጆች እያሏቸው በራህብ ምክንያት ቀያቸውን ትተው የሚሰደዱ ሺህ ወገን ያለን --- - እኛ
#ልቀቁልን ተብለው ከባዕታቸው የተነቀሉ ሁነኛም የሌላቸው የሚሊዮን ዕንባ ቤተኞች የሆኑ ወገኖች ያለን --- - እኛ ---
#በየዘመኑ በፖለቲካ ቀውስ የሚሰደዱ፤ የሚታሠሩ፤ የሚበተኑ ቤተሰቦች፤ የሚፈርሱ ጉልቻወች ያለን -- - እኛ ---
#በኑሮ ደረጃ በነፍስወከፍ ገቢ ከዓለሜ ይሁን ከአህጉራችን መጨረሻወቹ የአፍሪካ ተርታወች ውስጥ የምንገኜው -- እኛ
#በተፈጥሮ ይሁን በሰው ሠራሽ አደጋወች የወጣትነት ተስፋቸው ተጎሳቁሎ ሙሉ አካላቸውን ያጡ በርካታ ልጆች ያሉን ---- እኛ ---
#በአንድም በሌላም ሰርክ የትርታችን ትንፋሽ ሞት፤ መርዶ ስንቃችን እንዲሆን የተፈረደብን የዚህ ትውልድ ቤተኞች ---እኛ ---
#ለወቀሳ መቅድምነትን የምንሻ፤ ለመወቀስም ሽሽትን የምናጣድፍ እራሳችን በራሳችን የተቃረን - እኛ ……-
#ለውዳሴ፤ ለመሞካሸት፤ ለጭብጨባ ግን በጥድፊያ ላይ የምንገኝ ---- እኛ
#የትውልድ ማገዶነት ፈጽሞ የማይሰለቸን --- እኛው --
#ወጣት ጡረተኛ አብዝት የሚናፍቀን -- እኛ
#በግለሰብ ሰብዕና ግንባታ ላይ አቅማችን ሁሉ የምንደፋ፤ ለቋሚ ሰውኛ፤ አጽናኝ ቋሚ የተፈጥሮ ተቋማ ለመፍጠር የማንተጋው -- እኛ
#ሰውኛ ተብለን ተሸልመን፤ ባለማዕረግ ሁነን፤ እራሳችን ተፃረን የቆምን --- እኛ ---
#መጠሪያችን ማን ይሁን? መጠሪያችን ምን ይባል?
ትናት ጦርነትን ማቀድ መፈጸም -- ዛሬም ጦርነትን ማቀድ መፈጸም እንደ ትውልድ አባልነታችን አብረን ሁላችንም #ልናፍረበት የሚገባ የእኛው የራሳችን ገመናችን ነው።
#ዛሬ ዕንቅልፍ አልተኛሁም።
* እንዴትስ ዕንቅልፍ ይውሰደኝ?
** ሁልጊዜ ሃዘን?
*** ሁልጊዜ መርዶ፤
**** ሁልጊዜ ሰቀቀን፤
***** ሁልጊዜ ጭንቀት????
እራሳችን --- መምራት፤ ውስጣችን ማጽዳትም ማረም ያቃተን - እኛው፤
በመካሰስ ብቻ ዘመንን #በመሸንገል የክብር - የዝና - ምኞተኞች - ምቾቶኞችም --- እኛው???
ከሊቅ እስከ ደቂቅ እራሳችን ፈቅደን እስኪ --- እንፈትሸው? እስኪ ---- እንረመውም። #አረም አሳቦችን ከውስጣችን እናጽዳ። እግዚአብሄር የሸንጋዮች አይደለም። እግዚአብሄር የፃድቃኖችን ዕንባ ለመስማት ጆሮውን ያዘነበለ ቀን መካሰሱ ቀርቶ፥ ሁሉም እግሬን አውጬኝ ይሆናል። የፈጣሪ ውሳኔ ከሰው ልጅ #የስልጣኔ አቅም ነው።
* ቅንነትን ገፍተን፤
** ርህርህናን ገፍትረን፤
*** ሰውኛነትን አሽቀንጥረን፤
**** አይዟችሁ!------- ባይነትን አልይህ ብለን፤
****** አጽናኝነትን ተጠይፈን የምናተርፈው ብሩክ ትውልድ አይኖርም። እራስን ማዬት ውስጥን ለማረም መወሰን፤ ከራስ እራስን ሃግ ለማለት ከሊቅ - እስከደቂቅ የመወሰን አቅም ይኑረን። ዕውነት ከቦታው ለቆ አያውቅም። ዕውነትን - እንድፈር። ኢትዮጵያ የከበደችን ለሁላችንም ነው።
እንዴት አደራችሁልኝ ክብረቶቼ?
ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን።
ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።
ኑሩልኝ። አሜን።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©ሥላሴ
30/01/2026
ልቦናችን ሁሉ ወደ ሰላም ጎዳና ያቀና ዘንድ ፈጣሪ ይርዳን። አሜን።
ደክሞኛል።
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ