ፈረንሳይ {} ስፔን #ሁለት። ስፔን #ለዋንጫ እጮኛ ስትሆን ፈረንሳይ ደግሞ #ለደረጃ።

 

ፈረንሳይ {} ስፔን #ሁለት። ስፔን #ለዋንጫ እጮኛ ስትሆን ፈረንሳይ ደግሞ #ለደረጃ
 
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
 
የግማሽ ፍፃሜ ውድድር በዳህላስ 70ሺህ ተመልካች በተገኘበት የሁለት ምርጥ የአውሮፓ ቡድኖች ጨዋታ አንዱ #ለሙሽርነት ሌላው #ላጃቢነት ሁኗል መቋጫው። እቴጌ ድንቡልቡል #ማጫ እያማታች ነው። ሌላም እየጠበቀች ነው። ማጫው በለጥ ላለው፤ ጥሩ አድርጎ ላጎናት፤ ለሰለቃት ታደላለች። 
 
በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በከፍተኛ ራንክ ለዋንጫ የታጨው የፈረንሳይ ቲም፣ #ምን #እንደነካው አላውቅም በዛሬው በአገራቸውም ዛሬ ብሄራዊው #በዕላቸው ነው። ቀን ሳይቀናው ቀረ። ዛሬ ፓሪስ ምሽቱን እንዴት ታሳልፍ ይሆን?
 
የፈረንሳይ ቡድን እስከ 35ኛው ደቂቃ ድረስ #ምንም የግብ ሙከራ አላደረገም። አንድስም እንኳን። አይገርምም። በአንድ ጨዋታ ሦስት ጎል ያስቆጠረው ኮከብ አላቸው። ማፔም የተሰጠው ነው። በነፍስ ወከፍም በወልም ጠንካሮች ናቸው። ግን ዛሬ? 
 
ይልቁንም ከመጀመሪያው የውሃ እረፍት በፊት #ስፔን የቅጣት ምት አግኝቶ አንድ ጎል አስቆጠረ።
ከውሃ እረፍት እስከ ግማሹ መደበኛ እረፍት ጊዜ ድረስ ፈረንሳይ #ምንም ዓይነት የግብ ሙከራ ሳያደርጉ አንድ ለምንም ውጤት እረፍት ወጡ።
 
ከእረፍት መልስ የፈረንሳይ ቡድን ምንም ያሻሻሉት ነገር ሳይኖር ጨዋታው ቀጠለ። ስፔኖች አንድ መደበኛ የጎል ዕድል ቀንቷቸው #ሁለት #ለምንም መምራት ጀመሩ። በቀሪው ደቂቃ አካክሰው በአቻ ውጤት ጨዋታው ተራዝሞ ተጨማሪ ዕድል ይኖራቸዋል ብዬ ሳስብ፤ በመደበኛ የጨዋታ ጊዜ የዕለቱ ጨዋታ ተጠናቀቀ።
 
……… #ከዛስ? ትንሽ ልመለስ መሰል። 
 
ከዛማ በ64ኛው ደቂቃ አካባቢ ሁለተኛ ዕድላቸውን ፈረንሳዮች ሞከሩ። #አልተሳካም። የረባ ማራኪ የጎል ሙከራ አላደረጉም። ምን እንደሆኑ የሚውቁት እራሳቸው ናቸው። ብዙ ጊዜ ኳስ ይሾልክባቸው ነበር።
 
ስፔኖች በተደጋጋሚ #የማጥቃት #የመከላከል ተግባርን #አጣምረው ከወኑ። የስፔን ቡድን የተደራጄ ንቅናቄም ነበራቸው።
ፈረንሳዮች ምን እንደነካቸው አላውቅም። በጨዋታው አርትም፣ በኮኦርድኔሽንም፣ #በአትኩሮት ስስነትም በተጠበቀው ልክ አላየሁም።
ኮለንብያ እና ሲዊዝን የዳኙት የኤልሳባዶሩ ዳኛ ነበሩ የዕለቱ ዳኛ። 
 
#ግን ፈረንሳይ ሁለት ለምንም በስፔን?
 
ስፔኖች ጠንካራ ስልት እና ጥበብ አላቸው። ፈረንሳዮችም እንዲሁ #የሚናፈቅ የግል እና የወል አቅም ነበራቸው። ዛሬ ግን ቀኑ #ከዳቸው
በካታሩ ጨዋታ በሳምንት ሁለት ጊዜ ወደ ካታር ያቀኑት የፈረንሳዩ #ፕሬዚዳንት በዘንድሮው እስከ አሁን ትውር አላሉም። የፊፋ ፕሬዚዳንት ግን ነበሩ።
 
ግን የዛሬ ጨዋታ በከፍተኛ ጉጉት ተጠብቆ በጨዋታ መሳብ፣ ትዕይንታዊነት፣ ፋክክር የጠበቃችሁትን አገኛችሁን? ትሁታዊ ጥያቄ ነው።
ለእኔ #የበረደው #ድብ ያለ ነው የሆነብኝ።
 
ስፔን ለዋንጫ፣ ፈረንሳይ ለደረጃ #አንድ /// #አንድ ጨዋታ ይቀራቸዋል። ማፔ በካታሩ የዓለም ዋንጫ #ሁለተኛ መውጣቱ በእጅጉ አሳዝኖት ነበር። ዛሬ የባሰ ሆነ። ለነገሩ የወርቅ ጫማ ውድድሩን ይረታ ይሆን? 
 
ቸር አስበን፣ ቸር እንሁን። አሜን።
ቅን አስበን፣ ቀና እንሁን። አሜን።
ኑሩልኝ። አሜን።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ።
አሜን።
ሥርጉተ©ሥላሴ።
Sergute©Selassie.
14/07/026.
ኳሲዝም ለምልም።
See less

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።