24.11.2019 EC ለቆጠራ ዬተቀመርን።

 

 

ለቆጠራ ዬተቀመርን።
ፍቅር ነስቶን
ኢጎ አውሮን
ሰውሮን
በምንትሶ ተወረን
ተንተክትከን ወዬብን።
ተጣፍተን አጣፍተን
ማሰብን አደረግነው ገደል።
መኖር ጠፎቶን
ተስፋን ቀበርን።
ትዕግስት ነስቶን
ተነን።
መቻል አጥተን
ባከን።
ምንስ ብንሆን
ምንም።
በጭካኔ ሰግረን
በመታበይ እትብት ቆረጥን
ቂም ንብረት ሆኖ ቋጥረን
ጧ ብለን ተዘርግተን
ሟሟን።
ከእንፋቅቅ ጋር ተርትመን
በማነስ ተደምረን
በሽሚያ ደንብረን
በጥድፊያ ተሸርበን
በራስ ምልኪያ ተሸንሽነን
ተሸብልለን
ተቀሽረን።
በክፍፍል ሰክረን
በዲስኩር ብቻ አበድን
ዝለን በድነን
በራስ ፍቅር አረግን
እፍ ብለን በነን።
ተፈጥሮን ዘቅዝቀን
ባለማወቅ ቀበርን።
በምሻምሾ ተረት ተዛለን
ላሸቅን።
ኢትዮጵያ ለማለት እንሆ ተሳነን
ዛልን።
ግን ምንድን ነን?
እኮ ማነን?
የማን ነን?
ማንስ ነን?
ለማንስ ነን?
ለቆጠራ የተቀመርን።
ለማባያ የተሰበርን
ተአልቦሽ ነን።
#ሥርጉተ ሥላሴ። 11.33

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።