Danke, Schöpfer. Krieg ist das Bermuda-Dreieck. ተመስገን ፈጣሪ። ጦርነት ቤርሙዳ ትርያንግል ነው።
Danke, Schöpfer. Krieg ist das Bermuda-Dreieck. ተመስገን ፈጣሪ። ጦርነት ቤርሙዳ ትርያንግል ነው።…
ጦርነት ይቁም። ለምን? ሥልጣኔን ሥልጣኔ ሊያወድመው ስለማይገባ። (Der Krieg muss aufhören. Warum? Weil die Zivilisation des Friedens nicht durch die Zivilisation des Krieges zerstört werden darf.)
• ለሰው ልጆች ሁሉ፥ ለፍጥረታት ሁሉ፤ እንዲሁም ለተፈጥሮ እና ለስልጣኔም ለሁሉም የሰላም ነፃነት ሊሰጣቸው ይገባል። Allen Menschen, allen Geschöpfen, der Natur und der Zivilisation muss die Freiheit des Friedens gewährt werden.
« የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሄር
ግን አካሄዱን ያቃናለታል።» (ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፲፱)

የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት የጋዛን እና የእስራኤልን ጦርነት በዘላቂ ሰላም ለመቋጨት የተከበሩ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናል ትራንፕ ያቀረቡት ባለ 20 አንቀጽ ድንጋጌ በተመድ ዕውቅና ማግኜቱ እኔ እግዚአብሄርን አመስግኜበታለሁኝ።
በረከቱም ለራሺያ እና ለዩክሬን፤ ለሱዳን፣ ውስጥ ለውስጥ እየተብላላ ላለው የአፍሪካ ቀንድ፥ እንዲሁም ለእናት ኢትዮጵያ ይደርስ ዘንድ ምኞቴ ነው። ሥልጣኔን ሥልጣኔ ሊያጠፋው አይገባም። ሰላም ለው ልጆች ሁሉ። ሰላም ለተፈጥሮ።
Sergute©Selassie
18.11.2025
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።
-----------------------------------------------------
BBC
«የትራምፕ የጋዛ ዕቅድ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ድጋፍ አገኘ»
«የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታ ምክር ቤት የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጋዛ ያቀረቡትን ባለ 20 ነጥብ ዕቅድ የሚደግፍ የአሜሪካን ረቂቅ ውሳኔ አጸደቀ።
በዕቅዱ ውስጥ ዓለም አቀፍ የሚያረጋጋ ኃይል (ISF) መመሥረት የተካተተ ሲሆን፣ አሜሪካ እንደምትለው በርካታ ስማቸው ያልተጠቀሰ አገራት አስተዋጽኦ ለማድረግ ሀሳብ አቅርበዋል።
ውሳኔው ዩናይትድ ኪንግደም፣ ፈረንሳይ እና ሶማሊያን ጨምሮ በ13 አገራት የተደገፈ ሲሆን፣ ሀሳቡን የሚቃወም ድምጽ የሰጡ አገራት የሉም። ሩሲያ እና ቻይና በውሳኔው ላይ ድምጽ ከመስጠት ታቅበዋል።
ይህንን ውሳኔ መቀበል "የተኩስ አቁም ስምምነቱን ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ ነው" ሲሉ የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ቃል አቀባይ ተናግረዋል። ሐማስ ውሳኔው የፍልስጤማውያንን መብቶች እና ጥያቄዎች አላሟላም በሚል ውድቅ አድርጎታል።
ውሳኔው ከፀደቀ በኋላ በቴሌግራም ላይ ሐማስ ዕቅዱ "ሕዝባችን የሚቃወመውን በጋዛ ሰርጥ ላይ ዓለም አቀፍ የሞግዚት አስተዳደርን ያስገድዳል" ብሏል።
"በጋዛ ሰርጥ ውስጥ ለዓለም አቀፍ ኃይል ተግባራት እና ሚናዎች ሰጥቶ መመደብ፣ ትግሉን ትጥቅ ማስፈታት፣ ገለልተኛነቱን ማስወገድ እና ወረራውን የሚደግፍ የግጭት አካል እንዲሆን ማድረግ [ነው]" ሲል አክሏል።
በውሳኔው መሠረት የማረጋጋት ኃላፊነት አለው የተባለው ዓለም አቀፉ ኃይል (ISF) ከእስራኤል እና ከግብፅ ጋር በመሆን አዲስ ከተመለመለ እና ከሰለጠነ የፍልስጤም የፖሊስ ኃይል ጋር በመሆን የድንበር አካባቢዎችን ለመጠበቅ እና ሐማስን ጨምሮ መንግሥታዊ ያልሆኑ የታጠቁ ቡድኖችን በቋሚነት ትጥቅ የማስፈታት ሂደቱን ለማረጋገጥ ይሠራል።
እስካሁን ድረስ በጋዛ ያለው የፖሊስ ኃይል ሥራውን እያከናወነ ያለው በሐማስ ስር ሆኖ ነው። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአሜሪካ አምባሳደር ማይክ ዋልትዝ ለምክር ቤቱ እንደተናገሩት በጋዛ ይሰማራል የተባለው ዓለም አቀፍ የሚያረጋጋ ኃይል "አካባቢውን በማስጠበቅ፣ የጋዛን ወታደራዊ ኃይል የማስወገድ፣ የሽብር መሠረተ ልማትን የማፍረስ፣ የጦር መሳሪያዎችን የማውጣት እና የፍልስጤም ሰላማዊ ዜጎችን ደኅንነት የማረጋገጥ ኃላፊነት ተሰጥቶታል።"
የፀጥታው ምክር ቤት የፍልስጤም የሰለጠኑ ባለሙያዎችን፣ ከፖለቲካ ነፃ የሆነ ኮሚቴ አስተዳደርን የሚቆጣጠር እና የጋዛን መልሶ ግንባታ እና የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦትን የሚቆጣጠር የሰላም ቦርድ የተባለ የሽግግር አስተዳደር አካል እንዲፈጠር አጽድቋል።
በውሳኔው መሠረት ከሁለት ዓመታት የጦርነት ጊዜ በኋላ ጋዛን መልሶ ለመገንባት የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍ የሚመጣው በዓለም ባንክ ከሚደገፍ የትረስት ፈንድ ነው።
በውሳኔው መሠረት፣ ዓለም አቀፍ የሚያረጋጋ ኃይል እና የሰላም ቦርድ ከፍልስጤም ኮሚቴ እና ከፖሊስ ኃይል ጋር አብረው ይሠራሉ።
ትራምፕ የፀጥታው ምክር ቤትን ውሳኔ "ታሪካዊ" ሲሉ ጠርተውታል፣ እና ለሰላም ቦርዱ "ዕውቅና እና ድጋፍ" ለማድረግ የሚያስችል መንገድ ነው ብለዋል፣ የመጨረሻው አባላትም በቅርቡ ይፋ ይደረጋሉ። ሊቀመንበሩ ራሳቸው ትራምፕ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።
ትራምፕ "ይህ በተባበሩት መንግሥታት ታሪክ ውስጥ ከተላለፉት ታላላቅ ውሳኔዎች አንዱ ሆኖ ይቆጠራል፣ በመላው ዓለም ተጨማሪ ሰላምን ያመጣል" ሲሉ በ'ትሩዝ ሶሻል' የማኅበራዊ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል።
ከቀደሙት ረቂቆች በተለየ፣ ውሳኔው ወደ ፍልስጤም የራስን ዕድል በራስ መወሰን እና የአገርነት አስተማማኝ መንገድን ያመለክታል።
እስራኤል የፍልስጤም አገር መሆንን አጥብቃ ትቃወማለች፤ ይህም ወደፊት ግዛትነት በሚወስደው መንገድ ላይ ትልቅ እንቅፋት ነው።
ቁልፍ የአረብ አገራት የውሳኔውን አርቃቂዎች የፍልስጤም የራስን ዕድል በራስ መወሰን በጽሑፉ ውስጥ እንዲያካትቱ ጫና አድርገውባቸዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሐፊ ቃል አቀባይ ውሳኔው "... ወደ ተጨባጭ እና በአስቸኳይ ወደ መሬት ላይ ወደሚወርዱ እርምጃዎች መተርጎም" እና "የሁለት አገራት መፍትሄን ለማሳካት የፖለቲካ ሂደት" ማምጣት እንዳለበት አጽንዖት ሰጥተዋል።
አሜሪካ፣ የፍልስጤም ባለሥልጣን፣ ግብፅን፣ ሳዑዲ አረቢያን እና ቱርክን ጨምሮ በርካታ የአረብ እና የሙስሊም አብላጫ አገራት ውሳኔው በፍጥነት ተግባራዊ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።
የፍልስጤም ባለሥልጣን በሰጡት መግለጫ የውሳኔው ውሎች "በአፋጣኝ እና ወዲያውኑ" መተግበር እንዳለባቸው ተናግሯል።
በፍልስጤም ባለሥልጣን እና ሌሎች ስምንት የአረብ እና የሙስሊም አገራት ድጋፍ ስላደረጉ ሩሲያ እና ቻይና ድምጽን በድምጽ የመሻር አማራጮችን አልተጠቀሙም፤ ነገር ግን ውሳኔውን ከማጽደቅ ታቅበዋል።»
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ