#ሲቃ ስለ ህክምና ዋርካው፤ ፍቱኑ፤ ርትሁም ክቡር ፕሮፌሰር ዶር፤ ማለደ ማሩ።
#ሲቃ ስለ ህክምና ዋርካው፤ ፍቱኑ፤ ርትሁም ክቡር ፕሮፌሰር ዶር፤ ማለደ ማሩ። "አድርገህልኛል እና አመሰግንኃለሁኝ።" #ምዕራፍ ፲፰። ክቡርም፤ ልዑልም፤ ንጉስም ብለው የተገባ ነው። ተማሪ እያለሁኝ የኬሚስትሪ እና የባይወሎጂ ባለ100% ተማሪ ስለነበርኩኝ የህሊናዬ #ጽንስ የዚህ ታላቅ ሰው ጥረት እና ህይወት ነበር። ያን ጊዜ በዛች ትንሽዬ ወጣት ህልም የነበረው በዘርፋ ገፍቶ #ሳይንቲስት የመሆን የተልዕኮ ስንቅ ነበር። ግን የእቴጌ ጎንደር የአቀማመጧ ሁነት የከፋኝ ቤተኞችን ጋበዘ እና ባዕቴ የጦርነት ቀጠና ሆነች። ቤተሰብ ተሰደደ። ኃላፊነት በዛ ለጋ ዕድሜ ላይ ተጫነ። ህልሙም ተረሳሳ። ታናሽ እህቴን ተክቼ ትምህርቴን ለመቀጠል ሳስብ #ህወሃት ሥልጣን ያዘ። በቃ የትምህርት ናፍቆት ጋር መራራ ስንብት ሆነ። በስደቱም ታለመ ግን ፍጹም የማይቻል ሆነ። ጋሼን ተማሪ ሆኜ የህይወቴ #ሞዴል እንዳደረኩት አልቀረሁም። የሥራ ትጋቴ፤ ቅልጥፍናዬ፤ ሥራን ባዕቴ ማድረጌ፤ በዛ የወጣትነት ዕድሜዬ ወጣትነቴን ተላልፌ እራሴን ከርክሜ፤ ከብዙ ነገር ቆጥቤ መባተሌ እድገቴን ፈጣን አደረገው። ሥራዬ ከዚህ ታላቅ፤ ቅን፤ ጨዋ፤ ትሁት፤ ሰው አክባሪ፤ የጥረት #አብርኃም ጋር አገናኜኝ። በአካል ተገናኜን። የዕውነት የመማርን ልቅና በልዕልና ያዬሁበት ታላቅ የተግባር ዓራት ዓይናማ፤ ቅኔም ሰው ሆኖ አገኜሁት። ለዛች በዕድሜ፤ በተመክሮ፤ በዕውቀት፤ በሥራ ልምድ አናሳ ለሆነች ለግላጋ፤ ቁመቷ ዘለግ ያለች ወጣት የአገር ጉልላቱ ታላቅ ሰው ይሰጥ የነበረው አክብሮት #ዩንቨርስቲ ነበር። ከህሊና በላይ ነበር። ታናሽነቴን ስለማውቅ ከተቋሙ ጋር በሚያገናኙን የወጣት ማ...