ህግ አምላክ! እባከወት ይሁኑ በልከወት። "#ብሉ እዬተባለ ነው ያለና?" ከኡራኖስ የባጁት ቀዳማይ እመቤት ……

በህግ አምላክ! እባከወት ይሁኑ በልከወት። "#ብሉ እዬተባለ ነው ያለና?" ከኡራኖስ የባጁት ቀዳማይ እመቤት ……
ምን ብሉ?? ባሩድ? ጭንቅ? ጭፍለቃ? መፍረስ። መናድ? እራስን ማጣት። ብልኃት ዬሌለው ቅላት ትል ነበር እሚታዬ ጽግሽ።
በተጓዙ ቁጥር ጎንደር አዲስ ከንቲባ ይጠብቀወታል። አሁን 6/7 ኛው ከንቲባ ይሆናሉ። ለምን ብለው አጤወትን ጠይቀው አያውቁንም? ከ2015 ዓም ጥምቀት ማግስት ደግሞ አዲስ ከንቲባ ተመድበዋል ከብልጽግና ወንጌል። ወይ ጠቅልለው አባጠቅላዩ በሪሙት ኮንትሮል ከንቲባ ቢሆኑ ይሻላል። ሰርክ ከንቲባ ምርጫ???????
"ህግ ተላላፊወችን ጠላሁ"
እንሆ ………

 
ቤተ - ዬሻሸመኔ ዬእግዚአብሔር ዓውደ ምህረት በደም በጨቀዬ ፴ቀን ሳይሞላው ዬድፍረት ኃጢያት አዳመጥኩኝ።
"አቤቱ የድፍረት ኃጢያትን እንዳልሠራ ባሪያህን ጠብቅ።" አሜን
ንግግር አያስፈልግምፖ። #ሪባን መቁረጡ በቂ ነው። ቤተ - መቅደስ ተከርችሞ በዕለተ ሰንበት በመዲናዋ ሥርዓተ - ቅዳሴ፤ ሥርዓተ - ፍትኃት፤ ሥርዓተ - ተክሊል፤ ሥርዓተ - ቁርባን፤ ሥርዓተ - ማህሌት በጦር ኃይል ታግቶ መስቀል እዬተረሸነ፤ ለመሆኑ አዲስ አበባ ዬማን ናት አሁን? በትውስት እንደሚኖሩባትስ ያውቁ ይሆን???
፦፦፦፦ ነገ በኤሌትሪክ እጥረት፤ በውሃ አቅርቦት፤ በቀረጥ ጫና ለሚዘጋ ዕለታዊ ነገር ያለልክ እና ያለ ደረጃ በልቁ እና ዝልግልጉ የኦነግወኦህዴድ የቀውስ ፖለቲካ ተማምኖ ካለ ችሎታም፤ ካለ ክህሎትም እንዲህ ዘው ብሎ #ከመበለሻሸት #ዝምታ በስንት ጣዕሙ።
ሲሆን ሲሆን መናገር ዬማይችል ሰው አፅፎ ማንበብ። በስተቀር ከመቀስ ጋር ተዋውሎ በዝምታ እንደ ተከደኑ ይሻል ነበር። ትምህርት ቤት ዳቦ ቤት እዬሠሩ ማስመረቅ ይበቃወታል። እላፊ እባከወትን አይሂዱ።
ባለፈው ጊዜ ዬኢትዮጵያ ልጆች እናት እሆናለሁ ብለው የገቡትን ቃል በዓለም ዓቀፍ መድረክ መብላታቸው ዝም ስለተባሉ ይሆናል ይህን ያህል ባለቤታቸው ካቢናቸውን #ሱ! ጭጭ በሉ፣ ትንፍሽ ብትሉ ብለው ወዮ በማለት ቀጥረው በግል እንደሚያስተዳድር መቀጣጫ፤ ማስጠንቀቂያ እንደሰጡት፥ በኋላ ደግሞ ማጣፊያው አጥሯቸው በአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ አጥርነት ሲወድቁ ሲነሱ፣ አስታራቂ ነኝ ብለው ሲዳክሩ ተመለከትን።
ዬናቁት ይወርሳል ሆኖ ቅድስታችን ብድግ ቁጭ አሰኜቻቸው። ወሮ ዝናሽ ደግሞ በባዕታቸው ሂደው እርድህን - ተቀበል፤ በገዳ መዋጥህን - አጽድቅ፤ ግብርነትህን - ከብክብ ዳቦ ቤት ከፍተንልኃል ሲሉ #ተማፃዳቂ ንግግር አድርገዋል። ለዛውም ለጎንደር? ያን ጊዜ በዓለም አቀፍ መድረክ ንግግር ማድረጋቸውን ለእናቶች ሳጫውታቸው ከትከት ብለው ስቀው፥ "ለመሆኑ ንግግር ታውቃለችን? ብለውኝ ነበር። ለዛውም በጥዋቱ። ያውቃሉ አምን፤ ይለካሉ ይመዝናሉ።
ሰማዕቱ ኢኒጂነር ስመኜው ከመሰዋታቸው በዋዜማው ጎንደር ነበሩ ወሮ ዝናሽ ታያቸው። "ድህነትን አትከብክቡ" ሲሉ አዳምጬ ብሎጌ ላይ ጽፌ ነበር።
ምን አለ ዕድሜ ይንሳው እና ቲም ገዱ ሁሉንም አራግፎ፤ አሟጦ ባዶ ወና አስቀረው ተስፋችን። ወጣትነታችን የገበርንበትን ስልታዊ ተጋድሎ አፈር ድሜ አስግጦ ምድሪቱ አምስት ዓመት ሙሉ በደም ጎርፍ ተጥለቀለቀች። በጭንቅ ማጥ ሰጠመች፤ በሰበር ወጀብ ተለጋች።
#ዬተንጠራራው የቀዳማዊት እመቤት ዬወሮ ዝናሽ ታያቸው ንግግር ……
" ስንዴ አለን ለኤክስፖርት እያዘጋጀን ነው ብለዋል። …… እና መንግሥት ስንዴ ከሰጠ፤ ደግሞ እንዲህ አቅም ያለው ዳቦ ፋፍሪካ ሠርቶ ከሰጠ፥ ህዝብ እንግዲህ ብሉ እዬተባለ ነው ያለው እና በተቻለ መጠን ሰላማችሁን ጠብቁ፤ ሰላም እኔ ነኝ። ሰላም እናንተ ናችሁ። ሰላም ቤታችን ነው። ሰላም ከዬትም መጥቶ አይሰጠንም፤ በቃ እኔ እና እናንተ ብቻ ነን ምድሪቱን ሰላም ማድረግ እምንችለው እና አብዝታችሁ ሰላምን ብትፈልጉ፤ ሰላም ዬማይፈልጉ ህዝብን መረበሽ ዬሚፈልጉ ደግሞ አንዳንዴ በጣም አስባለሁ እና ትርምስምስ ሲሉ፣ እንሰሳ ተስማምቶ ይኖራል፤ ሲላመድ አንዱ ከአንዱ ተስማምቶ ይኖራል፤ እኛ ግን ተስማምተን መኖር አልቻልነም።"
ይህ ንግግር ለሜትሮፖል ደረጃን ለሚያሟላው ለጎንደር ህዝብ ነው። ይህችን ንግግር ናዝሬት ላይ፤ ነቀምት ላይ፤ ሻሸመኔ ላይ፤ ዝዋይ ላይ፤ ደብረዘይት ላይ ከአለቃቸው ከአቶ ሽመልስ አብዲሳ ፊት ቢያደርጉት መልካም ነበር። እዛው እደጃፋቸው ላይ ህፃናት በጅብ እዬተበሉ ነው በሸገር ፕሮጀክት፦ ግፋ ሞልቶ እዬፈሰሰ፦፦፦፦
በጣም ደፋር የሆነ ህዝብን ዬናቀ ዬወሮ ዝናሽ ታዬቸው የኢትዮጵያ ቀዳማይ እመቤት ያደረጉት ንግግር ፦፦፦ ባልተገባ መንገድ፣ ባልተገባ ወቅት፣ ካልተገባው ቦታ ላይ ዬተገኜ ነው።
እኔ እንኳን ከቁም ነገር ቆጥሬ አላዳመጥኩትም። አይቸዋለሁ ከመንግሥት ሚዲያ ፖስተሩን። ነገር ግን አላዳመጥኩትም። ከአዲስ ድምጽ ፎቷቸው ተለጥፎ ስላዬሁት ነው ያዳመጥኩት። አቤ በጣም በጥንቃቄ በአክብሮት ነው ይተው እባክወት ያላቸው።
እኔ ደግሞ ዘለግ አድርጌዋለሁኝ። ካለ አቅም እና ወርድ ፓለቲካ ውስጥ መዘፈቅ ልክን አለማወቅም ነው። "ትርምስምስ" ሲሉ ይሉናል። ወይ መዳህኒዓለም አባቴ??? ከዚህ በላይ ምድሪቱ ምን ትሁንላቸው ይሆን??? "ዬደላው ገንፎ ያላምጣል" ዬሚባለው ሆነ።
እኔ እና እሳቸው ተወልደን ያደግንበት ማህበረሰብ፤ ቤተሰባቸውም ጨዋ እንደነበሩ አውቃለሁኝ፤ "ልክን ማወቅ ከልክ ያደርሳል" ይላል። ምን አለ ምን አለ ወሮ ዝናሽ ታያቸው በዝምታ ቢተባበሩን ምን አለ?
ጎንደር ተጠርቶ ተጋብዞ እንኳን ጋዳ ነው። አንድ ዳቦ ቤት ከፍተው??? ይህን ያህል መስቃ??? ጭድ ቀርቦልኃል በሬ ሆይ አይነት እኮ ነው። አይገባም። ፀጥታቸው ይሻላል። ከተመቻቸው የደንም ቧንቧው።
ዬሆነ ሆኖ ጎንደር በምግብ ሙሊት ብቻ ሊመዘን? ለዛውም ዳቦ??? ሌላ አካባቢ ሙሽራ ካልመጣ ምግብ አይቀመሰም። ቡፌ አይጀመርም።
ይህ በጎንደር ፍፁም ነውር ነው። ጎንደር ሙሽራ አይጠበቅም። ተጋባዥ እንግዳው በመጣ ሰዓት ምግቡ ይቀርብለታል። ሙሽራ ከእንግዳ በላይ አይደለምና።
ሙሽራ ሲመጣ ማዕድ ቢባል ቢታሰብ ዬተጠራው ህዝብ ባዶ ድንኳኑን፤ አዳራሹን ጥሎላቸው ይሄዳል ለደጋሾቹ፤ እራሱ ጥሪ ወረቀቱ ሲሰጥ #አደራ እንዳይቀሩብኝ እዬተባለ ነው። የዋዛ ህዝብ አይደለምና። ቀድሞ ነገር መጀመሪያ ዬምናዬው የፊት ገጽን ነው። ከፍትፍቱ ፊቱ እንዲሉ።
እነ ኮነሬል ደመቀ ዘውዱ እርዱን ሲሉት "ከዬትኛው ዬፖለቲካ ድርጅት ጋር ነው የምትሠሩት ?" ብሎ በአደባባይ ጠይቋቸዋል። ዝም ብሎ ዘው ዬለም በጎንደሮች ቤት።
ከዛ እነሱ ዬማንነት እና የህልውና አስመላሽ ኮሜቴ እንጂ የዬትኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል አለመሆናቸውን ስለአተሙበት ያን መሰል ህወሃትን ከሥሩ የነቀለ ግሎባል አብዮት አካሄደ።
እስካሁን ድረስ ዬወልቃይት የጠገዴ የማንነት አስመላሽ ኮሜቴው በጀግና ኮነሬል ደመቀ ዘውዱ ዬሚመራው ዬዬትኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል አለመሆኑን አረጋግጫለሁኝ በግሌ። ለዛው እነ ወሮ ዝናሽን ለዚህ ዘመናይነት ያበቃው ተጋድሎ እስከዚህች ሰዓት ድረስ በጀት ዬለውም። በመላ ኢትዮጵያም አዲስ አበባን ጨምሮ ዬአማራ ነፍስ፤ ዬአማራ ኑሮ፤ ዬአማራ ህልውና ዬንብ ያህል ዋጋ ዬለውም። አንድም ዬአማራ ቁልፍ ታጋይ ዬነበረ ወሳኝ የፖለቲካ የብሄራዊ፤ ዬአህጉር፤ የግሎባል ቦታ ዬለውም። አንባሳደር አቶ ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከሥልካ።ካ።ጣን ዬተነሱበትም የዚያ አካባቢ ሰው በመሆናቸው ነው። ሌላ አንባሳደርም እንዲሁ ተነስተዋል። እንኳንስ ሌላ። ቋት የማይገፋ ትምክህት ዬራሴ መላጫ ነው።
ለአማራ ህዝብ ዬተረፈው ካቴና፤ መታፈን፤ መታገት፦ መታረድ፤ ለጦርነት መማገድ፤ በትምህርት፤ በሥራ፤ በዕድገት መፈናቀል፤ መስቀል አስሮ አዲስ አበባ መኖር እንኳን አልተፈቀደም። የአማራ ፀሐፍት፤ የአማራ ዬፖለቲካ #ሊቃናት፤ ዬአማራ የፖለቲካ #ሊሂቃን፤ የአማራ ከያንያን፤ ዬአማራ እጩ ሊቃናት፤ ዬአማራ ጽንስ ሳይቀር እዬታደነ መዳረሻ አጥቷል።
ስለ ሰላም ቀዳማዊቷ ሲሰብኩ "እኛ እና እናንተ ነን ሰላምን ማምጣት እምንችለው" ብለዋል። አንባቢ ከሆኑ የሞገድ ጋዜጣን ይግዙ እና ያንብቡ። ያ ልበወለድ ታሪክ አክተር ትዳራቸው ነው። ቀውስ ጠንስሰው፤ ቀውስ አደራጅተው፤ ቀውስ መርተው፤ ቀውስ ሲጠጡ ውለው የሚያድሩት ባለቤታቸው ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ናቸው። እኔ ጥሩ ሥም አግኝቸላቸዋለሁ። ሙሉ አምስት ዓመት ታዝቤ። #አሳቻው #ቤርሙዳ ትርያንግል ብዬ። ቅጽበትም ናቸው። ቀውስም ናቸው። ሰበርም ናቸው። ግራጫማ ሲቃም ናቸው።
ከሻሸመኔው የደም ንክር ማግሥት በደም ዘልበው ጣልያን፤ ማልታ፤ ፈረንሳይ ሄደው ከመሪወች ጋር ሲዘባነኑ፤ ሰሞኑን ከዓለም እና ከአፍሪካ መሪወች ጋር ምንም እንዳልተፈጠረ በድግሥ በግብረ ሰላም ሲቀማጠሉ፤ ሠፈራቸውን መምራት ሳይችሉ ስለ ፓን አፍሪካኒዝም ሲደሰኩሩ ሰው ስለመሆናቸው እጠራጠራለሁኝ። እሬሳ እንኳን መስጠት አይፈቅዱም።
ለነገሩ አብረው ለበሉ ለጠጡት ለቲም ዶር አንባቸው መኮንን እንኳን አልሆኑም። ምን አልባት ቀዳማዊት እመቤት ወሮ ዝናሽ ታያቸውም ተራቸውን ለስንብት በደራሽ ዜና እናዳምጥ ይሆናል። ማን ያውቃል? እሳቸውም አንድ ቀን እዬጠበቁ ይሆናል። እፋኝት ሲረገዝ አባቱን ሲወለድ እናቱን መግደል ልማዱ ነውና። ለነገሩ እሚረብሹ አሉ ሲሉ ጤናቸውንም ተጠራጥሬያለሁኝ። የሳቸው ሞድ እና ግብረ ሰላም ዬመኖር ዋስትና የሰጠ ይመስል። ከአዲስ አበባ ወደ ሌላ ለመጓዝ አማራጩ አውሮፕላን ብቻ ሆኗል። አዬር መቃወሚያ አቶ ጃል መሮ እስኪበረከትላቸው ድረስ። በጣም የተቀናጣ ንግግር ነው ያደረጉት።
አንድ ታሪክ ላጫውታችሁ ጎንደር ጡሮታ ሰፈር ዬሚባል አለ። ዝቅተኛ ማህበረሰብ ይኖርበታል። ትንሽቷ ኢትዮጵያ ነው ሁሉም ማህበረሰብ በፍቅር አብሮ ይኖራል። የሚናፈቅ ቦታ ነው። ከሠራዊት በጡሮታ ዬተሰናበቱ ወገኖች ይኖሩበታል። የደላቸው ደልዳላ እመቤት እዛ ይኖሩ ነበር። ሥም መስጠት ተገቢ አይደለም። ለቅሶ ሲኖር በሠራተኛ እንጀራ እና ወጥ እያስያዙ ይልካሉ።
ከዕለታት አንድ ቀን ዬደልዳዋ ወሮ ባለቤታቸው አረፋ። ያ ግቢ በሞት ተደፈረ። ቤታቸው ግቢው በቆርቆሮ ዬታጠረ ነው። ዬሃብታም ነገር ዘንከት ያለ ድንኳን ተጣለ። ማታ አስተዛዛኝ ሲጠበቅ ሰፈርተኛው በልጁ እያስያዘ እንጀራ እና ወጡን ላከ። ወይዘሯዋ ባዶ ድንኳናቸውን አሳቅፎ ነዋሪው በዝምታ ቀጣቸው። ከዛ ደልዳላዋ ወሮ ከህዝቡ ጋር ተቀላቀሉ። ዬዕውነት ታሪክ ነው ዬምነግራችሁ። ጎንደር በዝምታው ውስጥ ተዘርዝሮ ዬማያልቅ ዕምቅ አቅም ያለው ማህበረሰብ ነው። ዳኛም ነው። የፍትህም አደባባይ።
ለዛውም ለሆድ???? ጎንደር? ህም። በሞቴ አፈር ስሆን እኮ ፍጥረተ ነገሩ ከዛ ዬጥሞና አቅም የመነጨ ነው። ለፍርፋሪ፤ እና ለቅርጥምጣሚ ደንታ እንደሌለው ያውቁታል። #መብቱን #ለችሮታ ዬሚገብር ህዝብ አይደለም። ፈጽሞ። ለቀዳማዊ እመቤትነት ከሆነም እቴጌ ተዋቡ፤ እቴጌ ምንትዋብ፤ እቴጌ ጣይቱ፤ ከንቱዋ ወሮ አዜብ መስፍንም ነበሩ እኮ??? ብርቁ አይደለም። ለዛውም በክህደተ - ኢትዮጵያ፤ በፀረ - አማራ፤ በፀረ - አማርኛ ቋንቋ፤ በፀረ - ዬኢትዮጵያ - ኦርቶዶክስ፤ በፀረ - ሰው፤ በፀረ - ተፈጥሮ፤ በፀረ - ንፁሁ አረንጓዴ ቢጫ እና ቀይ፤ በፀረ ግዕዝ፤ በፀረ ቀደምት ታሪክ እና ትውፊት የተከዘነ ሥርዓት ትቅቅፍ ናፍቆተኛ ሊሆን ቀርቶ።
#ስንዴውን በተመለከተ ……
በነገራችን ላይ ጎንደር የማይመረት የእህል፤ ዬቅመማቅመም ዘር ዬለም። ገብስ እንኳን ሰምታችሁት ዬማታውቁት ዬገብስ ዝርያዋች ከአምስት በላይ አሉት፤ ስንዴ በጣም አምራች ነው ወገራ። እና ብርቁ አይደለም። እስቅ ነበር ለመላ ኢትዮጵያ ኦሮምያ ስንዴ ያመርታል ሲባል። ዬሆነ ሆኖ በኦሮምያ ገበሬወች ሌላ ምርት እንዳያመርቱ ታግተው በግዳጅ ዬተከወነ ነው። ይህን ልጅ ተክለሚኬኤል አበበ ሲገልጥ አድምጫለሁኝ። ገበሬወች ድንች ማምረት ፈልገውም እንደታገዱ፤ ዬስንዴም ኮንትሮባንድ እንደአለ። ዬሚገርመው ጆንያውን እንኳን ለውጭ አገር ቀርቶ እዛው ለአገር ውስጥም አይሆንም። ዬተቀዳደ ነው።
በዛ ላይ ከ20-30 ሚሊዮን ዬሚጠጋ ህዝብ ዬዕለት ደራሽ ምግብ ይሻል ኢትዮጵያ ውስጥ። ከሱማሌ ላንድ ወደ 50 ሺ ተፈናቃይ ወደ ኢትዮጵያ እዬጎረፈ ነው። በዓለም በአገር ውስጥ መፈናቀል ኢትዮጵያ ሪከርድ በጥሳለች። እዛው እጓሯቸው ሸገር በሚል ፕሮጀክት ሺወች ሜዳ ላይ ወድቀዋል። በጅብ ዬተበሉ ህፃናት አሉ፤ በአማራ ክልል ብቻ ሚሊዮኖች ሜዳ ላይ ናቸው። እራሱ የሎቢ ሥራ ለመሥራት ጽሁፍ ለማቀናበር ይቸግራል። እራስ እግሩ ችግር ስለሆነ ዬቱ ላይ አተኩረን እንፃፍ? ዬችግር ናዳው ስለአዬለ።
#የዳቦ ጉዳይ ከተነሳ ……
ዬገብረማርያም ዳቦ በዶልች ሻይ፤ የህብስት ዳቦ፤ ዬሙጌራ ዳቦ ብርቁ አይደለም - ለጎንደሬ። ይህም ሆኖ የዳቦ ፋፍሪካ ዬከፈቱ ወጣቶች ትርፋ 50 ሺህ ቢሆን ቀረጡ 80 ሺህ ዬሆነባቸው፤ በውሃ እና በኤሌትሪክ እጦት ዬተዘጉ በኪሳራ ዳቦ ቤቶችንም ያውቃል ጎንደር። በጥቃቅን እና በአነስተኛ ዬተደራጁ ከገብያ ውጭ ሆነው፤ ዲግሪውንም የሙያ ይዘው ዬተሰደዱ ልጆች አሉት። ጣና እናቱ ከቅርብ ነው። ግን በውሃ ጥም ይሰቃያል - ጎንደር፤ በቀደመው ጊዜ ትግራይ ሲበራለት መንገዱን ጠባቂው ግን ብርሃኑ አልፎት ሂዶ ነበር። ዛሬም መዳከር ነው። 30 ቀን ኤሌትሪክ ሳይቋረጥ፤ ውሃም ቧንቧ ውሃ ሳይታጣ ከቀጠለ እስቲ ይታያል። በኽረ ችግር መፍቻው የለብ ለብ አንቲ ፔን ሳይሆን ሰውኛ ዬሆነ መኖርን በነፃነት የሚያኖር ፕሮጀክት ነው ጥሩ።
#ጓዘ ቀላል ጥያቄ ለቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ……
እስከመቼ ነውስ አቶ ጃልመሮ ወይንም አቶ ጃል ሽመልስ አብዲሳ ቤተ - መንግሥቱን ለአማራዊቷ ቀዳማይ እመቤት እና ልጆቻቸው የሚፈቅዱላቸው??? ያው "ቤተ ቁሞ ቀር፤ የተሰበሩት ትምክህተኞች" ቤተኛ ስለሆኑ ……… ሌላ ቤተሰበወት ከጎንደር ተነስተው ባህርዳርን፤ ማርቆስን፤ ዳንግላን፤ ዬማንኩሳን ኮኮ እና ሙዝ እዬተመገቡ ዬጎጃምን ዬጤፍ ዞሞ እዬቃኙ አባይን ተሻግረው ጎኃ ጽዮን፤ ዬገብሬጉራቻን ቅምጥል ቅቅል ተመግቦ በቸር አዲስ አበባ መግባት ይችላልን? ዬአዲስ አበባ ነዌ።ዋሪስ ዝዋይ ቤተሰባቸውን ይዘው ዘና ለማለት ይችላሉን በተለይ አማራ ከሆኑ???? ዬትኛውን አገር ይሆን እያስተዳደራችሁ ዬምትገኙት።
ባለቤተወ ወደ ስልጣን ሲመጡ ስለ ደቡብ ሱዳን ዘለግ ያለ ሃሳብ አቅርቤ ነበር አልሰሙሜ። አሁን ወደ 200 ኪሜ ዘልቀው ገብተው ወረዳ ሰይመዋል፤ የጋንቤላ ልጆችም ይታገታሉ፤ በስሜንም ከ70 ኪሜ በላይ ሱዳኖች ይዘዋል፤ ትግራይ፤ ወለጋ ያሉበት ይታወቃል። አካ።ጣዬ 10 ጊዜ ነዳለች እና አላችሁን???? ስለ ሰላም ለመስበክ አቅም አለን????
#ማጠቃለያ አይነካኩን።
እንደምን ከሥሩ ህወሃትን መንቀል እንደተቻለ ለምናውቅ ሞጋቾች #ጥሙርሙር ፖለቲካ አምጥተው ባያምሱን ሸጋ ነው። ስለማይችሉን። አንመጣጠንም። ቀዳማዊቷ ጠረናቸው ዘመናይነትን ቢጠዬፍ መልካም ነው። ስንት ሚሊዮን ደመከልብ ህዝብ ዙፋን ላይ ተቀምጦ "ሰላም" የሚለውን ቅዱስ ቃል ጣልቃ ባያስገቡት። ትሬፓ አያድርጉት። #ክህነቱንም ለተሰጣቸው መድረክ ያድርጉት። ይህንንም ጎንደር እንደምን እንደሚጠዬፈው ያውቁታል ክህነት - ለሴት???
ከዛ ከሊቅነት ከጨመተ ዬሊቀ -ሊቃውንን ቤተ መፃህፍተ ትርጓሜ ጉባዔ ባዕት ላይ መቀናጣት እንዲህ አያስፈልግም። ዬብሉይ፤ ዬአዲስ፤ የመነኳሳት፤ ዬአቋቋም፤ ዬዜማ፤ ዬቅኔ ምንጭ አውራ ላይ? ዓራት ዓይናማ ተናጋሪ ያፈራ ባዕትም ነው። የታሠረ አንደበት ያለው ደግሞ ዝም ማንን ገደለ? አሁን በእርስወ ንግግር ተማርኮ ህልውናውን አሳልፎ ሊሸቅጥበት??? ያውቁታል።
በመጨረሻ ጨካኙን ባለቤተወትን #ሃግ ይበሉ ሰውነትን የማክበር ተፈጥሮወት ካልተነነ። ጭካኔን አቅፎ መቀጠል ኃጢያትም ነው ለካህኗ ቀዳማይ እመቤት። በሰመጠ መርከብ እንዲህ በትርፍ ንግግር ከሚያቆሳስሉን ቢተውን። ደግሜም እናገረዋለሁ አይችሉንም። እኔ እበቃወታለሁኝ። ሌላም አያስፈልግ። ይተውን።
ሲሆን ሲሆን ግራ ቀኛችሁ ኢትዮጵያ ስለከበደቻችሁ በፈቃድ ለሚችል እንደ አቶ ኃይለማርያም ደሴ ብታስረክቡ። ካልተቻለም በዝምታ ይተባበሩን። እባከወትን? ግፍም ነው። አንድ ቀን በአዘኑ፤ በተጎሳቆሉ፤ ሜዳ ላይ በወደቁ ሚሊዮን ምንዱባን ድንኳን ተገኝተው ያላፅናኑ፤ አይዟችሁን ያልቀለቡ በሽርሽር እና በሞድ ክብር ማማ ላይ ዬተቀመጡ ልዕልት እባከወ ይተውን። አይችሉንም። አቅመወትም አይደለም ፖለቲካ።
ብዙ ሰው መሪ ሊሆን ዬሚችል ኢትዮጵያዊ እንደሌለም ይገልፃል። የፖለቲካ ድርጅት ነው የሌለው እንጂ መሪ ዬሚሆኑ ኢትዮጵውያን አሉ። በሌላ በኩል ለውጡ በኦሮምያ ንቅናቄ እንደመጣ በመታበይ ሲገልፁ እሰማለሁኝ፤ ጠቅላዩም እንደምን ለውጥ እንደመጣ እናውቀዋለን አልፈንበታል ሲሉ አዳምጫለሁኝ። ሌላ አዲስ መንገድ ተከተሉ ሲሉም እሰማለሁ ዶር አብይ አህመድ። ተደክሞ ለኦነግ ስለተሰጠ ብቻ ነው ዝምታችን እንጂ ህወሃት ከሥሩ የተነቀለበት መሳሪያ ጥበቡን የፈፀሙትም ያስፈፀሙትም ያውቁታል። እና መስቃውም፤ ትምክህቱም በልክ ይሁን። ግን ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ካለ ቀጠሮ በደራሽ እስራኤል ከባህርዳር ሰማዕታት በቿላ ለምን በረሩ? ምን አራወጣቸው? እንተዋወቃለን።
ሌላ ይሉኝታ ዬሌላቸውን ባለቤተወትን ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድን ይጠይቋቸው ስለምን 50% ዬሴት ካቢኔ ማደራጀት እንዳአሰኛቸው? ሚስጢሩን እሳቸው ያውቁታል። ዬማንን ልብ ሰልበው ሥልጣናቸውን ማደላደል እንደፈለጉ። መሰረታዊ የትግል አቅጣጫው ተጠልፎ ነው ይህን ያህል ትውልድ በሰኔል እና በቹቻ ሽኝት ዬዋይታ ዘመን ዕድሜውን፤ መኖሩን እዬተዘረፈ ዬሚገኜው። እ
እግዚአብሔር ይስጥልኝ።
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
23/02/2023
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።

 

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።