ዕለተ - ትውልዱ 20.12.2019

 

ዕለተ - ትውልዱ።
በቅንጅት፣ በሰማያዊ ፓርቲ የተሰው። ሁለቱም ፓርቲዎች ሞተዋል። የህግ ባለሙያው ሰማዕት ሳሙኤል አወቀ እና እጩ ሊቅ ሰማዕት ሺብሬ ደስአለኝ ግን አልፈዋል።
ለማይዘልቅ ዓላማ፣ ለማይዘልቅ ግብ፣ ለማይዘልቅ ራዕይ። ትውልዱ በዚህ ይለካል። መገበሩ ያለትርፍ። ነገም ይኽው ነው።
አሁንም ከተንበጫበጨ ዘመን ላይ እንገኛለን። መላቅጥ ውሎ ጉዞ የሌለው። የደላቸው ይኖራሉ። እነሱ ዕለታዊ ናቸው። ስለትናንት፣ ስለ ነገ ግድ የማይሰጣቸው።
እንደ አገር እንደ ትውልድ ሲታሰብ ግን ትውልድ ተገብሮ ትውልድን ከግብርነት የሚያስቆም ሥርዓት ማፊ ነው።
ማስተዋል ተሰዷል። ከትናንት እስከ ዛሬ ለአንድ ዕጣ ነፍሥ ሥም፣ ዝና ሲባል ትውልድ በራህብ አንጀቱ ይማገዳል። አስታዋሽ የለውም። ቤተሰብ አምጦ ይወልዳል፣ አምጦ ያሳድጋል እንደ አማጠ ያልፋል።
ይህን መከራ ኃላፊነት ወስዶ መልክ ማስያዝ ይቻል ነበር ግን በሩ ተከርችሟል። ውድቀት ክብር ሆኖ ይፎከራል። ትውልድ ያለቀበት የዴሞክራሱ ጥማት ዛሬም ቀራንዮ ላይ ነው።
ድቀት - ስብራት - ውርዴት እንደ ልዕልና ሲንጨበጨብለት መርኽ ተምሶ ሲቀበር ከማዬት በላይ የቁም ሙትነት የለም። እያለን የለለን፣ እዬፈሰስን ያለቀን። እግዚአብሔር ይስጥልኝ።
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።