"እንዳያማም ጥራው፤ እንዳይበላም ግፋው።" ለሰብ ትርታ #መደንገጣችሁን እስከ ምን ይጠበቅ?
"እንዳያማም ጥራው፤ እንዳይበላም ግፋው።" ለሰብ ትርታ #መደንገጣችሁን እስከ ምን ይጠበቅ? "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን። • ቅኒትን፤ የልቅና ባለቤቷን፤ የዊዝደም ጉልላቷን ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደረጃዋ ይህ ነውን? https://www.youtube.com/watch?v=uBHU_VSzGhQ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ #ምዕራፍ ፲፱። ከኢትዮጵያ መንግሥት የተሰጠውን መግለጫ አዳመጥኩት። አገርን - በቅንነቷ፤ በዊዝደሟ - ልዕልና፤ በመንፈስ #ንጽህናዋ ልክ መሠረት ያስያዘች ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ #ዕንባ በምን መልኩ እንደሚታይ ሙሉ ፰ ዓመት አይቻለሁ። አድምጫለሁኝ። ለእኔ ምንም አዲስ ነገር የለውም። ምን አልባት "እንዳያማም ጥራው …"የመግለጫው ዓይነት ይሆናል አዲሱ። በሌላ በኩል ብሄራዊት፤ ዓለም ዓቀፋዊት የሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶም ሊቃናት፤ ሊሂቃን፤ የተደራጄ መዋቅር፤ ቀኖና እና ዶግማ ያላት ተቋማዊ ሃይማኖት ናት። የቅድስቷ #ነቁጧ ብቻ የሚስጢር ዲካዋ ሊሠፈርም ሊለካም አይችልም። ፈተናዋም የዚያኑ ያህል ዲካ የለሽ ነው። እራሷን የቻለች፤ ሁሉ ያላት፤ የምትችል ሆና ግን የዝምታዋ #መንገሥ ልጆቿ የየለት ሰማዕትነት፤ የተቋማቷ ስደት፤ የሁለመናዋ ተከላካይ አልባ መደፈር በበዛ ትዕግሥት መያዟ ፈተናዋ መቋጫ አጣ። የእኛ የታናናሾቿ ዝምታም ልኳ፤ ልዕልናዋ፤ አቅሟ፤ ልቅናዋ የማይደረስበት በመሆኑ በደል ሲጠናባት ዕንባችን አፍስሰን ተማጥኗችን ለላይኛው እንልካለን። አጽናኟ፤ አይዞሽ ባዮዋ ቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ፤ እንዲህ ለራሷ መሆን ሲሳናት ማዬት እጅግ ያሳዝናል። በማናቸውም ብ...