ልጥፎች

#ኢሠመኮ የት ነው ያለው? የተቋሙ #ነፍሱ አለን? ለመሆኑ አዲሱ የኢሠመኮ አመራር #ይተንፍሳልን???

ምስል
  #ኢሠመኮ የት ነው ያለው? የተቋሙ #ነፍሱ አለን? ለመሆኑ አዲሱ የኢሠመኮ አመራር #ይተንፍሳልን ???    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።         የሁሉም በሽታ መነሻ የአንጀት ጉዳይ ይመስለኛል። አንጀት ደህና ከሆነ ሌላው አካልም ደህና ይሆናል ብየ አምናለሁኝ። የአንጀት በሽታ ከባድ እና ውስብስብ ነው። የአንጀት በሽታ መለያው ገረጭራጫ የሆነ #ባህሬ #ቢስም ነው። የአንጀት በሽታ #ጠቡ ከምግብ እና ከመጠጥ ጋር ነው። ካልተበላ እና ካልተጠጣ ደግሞ የሰው ልጅ ህይወቱ አይቀጥልም። አንድ የአንጀት በሽተኛ #ይርበዋል ። ሲበላ ደግሞ ስቃዩ ይጨምራል።    አንድ የአንጀት በሽተኛ ይጠማዋል #ሲጠጣ ደግሞ ሌላ ተጨማሪ ስቃይ ነው። አንድ የአንጀት በሽተኛ በተሟላ ኑሮ እንኳን እያለ #ያሻውን አይመገብም። ሁልጊዜ ታጥቆ ስንዱ ሆኖ #በጥንቃቄ ነው የሚኖረው። አንድ የአንጀት በሽተኛ ሲጓዝም ከመገብ ይልቅ #እርሃቡን ይመርጣል። ስቃዩ #አሰቃይ ነውና።   በዚህ ላይ የሃኪም ክትትል #መከልከል ፤ በተጨማሪም ውስብስቡ የእስር ቤት ህይወት ጋር #የአንጀት ህመም ፈታኝ ገጠመኝ ነው። ስቃዩን የሚያውቅ ያውቀዋል። እስር ቤት ሆኖ የአንጀት በሽተኛ መሆን የቅጣቱ መልክ እና ይዘት እጅግ #የከፋ ይሆናል።   አባት ታዲዮስ ታንቱም #የአንጀት በሽተኛ ናቸው። ቆሎ ብቻ ይመገቡ እንደ ነበር ባለፈው ከእስር ሲፈቱ ሲገልጹ ሰምቻለሁኝ። ቢያንስ እስር ቤት ለሚገኙ፤ በእጁ ላይ ባሉ ህሙማን #እርህርህና በአንድ መንግሥታዊ ሥርዓት ውስጥ ስለምን #እንዲሰደድ ይፈቀድለታል። አንድ ህሙም ስለምን ህክምና #ይነፈጋል ? ለምን? ሰው በአገሩ መንግሥት የህክምና አገልግሎት ሳያገኝ ተጨማሪ...

ለቀጣዩ ትውልድ ከልብ #ከውስጥነትም የማሰብ ጸጋ እንዲህም ይገለጣል።

ምስል
  • ለቀጣዩ ትውልድ ከልብ #ከውስጥነትም የማሰብ ጸጋ እንዲህም ይገለጣል።   https://www.bbc.com/amharic/articles/cwydn14d4pyo «ትራምፕ ኦቲዝም ያስከትላል ያሉትን መድኃኒት ነብሰ-ጡር ሴቶች እንዳይወስዱ አሳሰቡ» የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ ዶክተሮች ለነብሰ-ጡር ሴቶች ታይሌኖል የተባለውን ማስታገሻ መድኃኒት እንዳይሰጡ አሳስበዋል።»   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።     ይህ ለቀጣዩ ትውልድ ከልብ ከውስጥም የማሰብ ጸጋ በእጅጉ #መሰጠኝ ። ስለሆነም ሼር አደረግኩት። በትውልድ ጉዳይ ላይ ጤነኛ ሃሳብ የሚያቀርቡ ሁሉ ለእኔ #ብጹዓን ናቸው። እንደ #ተራራው #ስብከትም ነው የማየው።   ዛሬ በዓለማችን ጎልተው ከወጡት ችግሮች ውስጥ እጅግም አሳሳቢው ጉዳይ፤ የህፃናት ተስፋ አብረው #በሚወለዱ መንፈሳዊ፤ አካላዊ ጉዳቶች መሰቃየታቸው ነው። ይህ አዌርነስ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላው ዓለም የሚገኙ ሴቶች ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ከውስጥ፤ ለውስጥ የተላከ #ቅዱስ #መልዕክት ነው።   በዘርፋ ላሉ ተመራማሪወችም፤ ፈላስፎች #አዲስ #በር የሚከፍት ይመስለኛል። በሉላዊ ደረጃ ከተደማጭ ሰብዕና የፈለቀ ሃሳብን #ባሊህ የሚሉ በርካታ ልባሞች ዓለማችን አላት እና።    ስለሆነም ኢትዮጵውያን ሃሳቡን #ከልብ #ቢያዳምጡት ጥሩ ይመስለኛል። "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።" ይላል አካል የሌለው የእግዚአብሄር ትጉህ አገልጋይ ቃለ ወንጌል።   በሁሉም ዘርፍ ከመውለድ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ጥንቃቄ የኢትዮጵያ ሴቶች እንዲያደርጉ ቤተሰብ፤ የትዳር አጋር፤ በዘርፋ ያሉ ባለሙያወች ሁሉ ሃሳቡን ሳያጣጥሉ ከ...

ውስጠ ቃናው ሰውኛ የሆነ መንፈስ ....

 ውስጠ ቃናው ሰውኛ የሆነ መንፈስ ቀን ከሌት የሚያስበው ስለ ሰው ልጅ #የመንፈስ #ጤንነት ነው።  ለዚህ ደግሞ #ቀና ልቦና እና #ቅንነትን ይጠይቃል።  ይህን ለማድረግ #የውስጥ #ፈቃድ ብቻ ነው የሚያስፈልገው።   #ቅን እና #ቀና መሆን ወጭ የለውም። ውጣ ውረድም የለውም።  ቅርጥምጣሚ ፈተናወች ይገጥማሉ እነሱንም #አጤ #ቅንነት የመቋቋም ሙሉ አቅም አለው።  ውድ ቤተሰቦቼ እንዴት አደራችሁ። ኑሩልኝ --- በቅንነት። አሜን።  ሥርጉትሻ 2025/09/22

#የፈቃድ ጉዳትን ፍቀደው እና ተዋወቁ።

  #የፈቃድ ጉዳትን ፍቀደው እና ተዋወቁ። #ቸር ሁን እና ተጎዳ።   #ሩህሩህ ሁን እና ተጎዳ። #አዛኝ ሁን እና ተጎዳ።   #አጽናኝ ሁን እና ተጎዳ።   #አይዟችሁ ባይ ሁን እና ተጎዳ።   #ቅን ሁን እና ተጎዳ።   #ዕውነተኛ ሁን እና ተጎዳ።   #የመርኽ ሰው ሁን እና ተጎዳ። #ታጋሽ ሁን እና ተጎዳ።   #እዩኝ እዩኝ አትበልና ተጎዳ። #ህግ አክባሪ ሁን እና ተጎዳ።   #ርጉ ሁን እና ተጎዳ። #ቅጽበታዊነትን ተጸየፍ እና ተጎዳ።   #ሰውኛ ሁን እና ተጎዳ። #ተፈጥሮኛ ሁን እና ተጎዳ።  ደስታ #መጋቢ ሁን እና ተጎዳ። ቂመኛ #አትሁን እና ተጎዳ።  በቀለኝነትን #ተጠየፍ እና ተጎዳ።  ብቁ #አድማጭ ሁን እና ተጎዳ።  ትሩፋትህ መንገድህ የቀና - የውስጥ ሰላምህ የከበረ - ንዑድ ህሊናህ ለችሎት የማያቀርብህ ትሆናለኽ። ሥርጉትሻ 2025/09/17

"#ፕሮፌሰር ዶር ብርሃኑ ነጋ "ጉራጌ ስለሆኑ ወጀብ በዛባቸው ያልከው" በፍጹም #አይመስለኝም - ለአቶ ኤርምያስ ለገሰ።

  " #ፕሮፌሰር ዶር ብርሃኑ ነጋ "ጉራጌ ስለሆኑ ወጀብ በዛባቸው ያልከው" በፍጹም #አይመስለኝም - ለአቶ ኤርምያስ ለገሰ።    "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን!     ጤና ይስጥልኝ አቶ ኤርምያስ ለገሰ እንደምን ሰነበትክ? ሁለቱንም በፕሮፌሰር ዶር ብርሃኑ ነጋ በግልህም ለሁለትም ሆናችሁ ያደረጋችሁትን ውይይት አዳመጥኩት። ስለምን በፕሮፌሰር ብርኃኑ ነጋ ላይ ወጀብ በዛ በሚለው አመክንዮ የሰጠኽው አስተያዬት " ፕሮፌሰር ዶር ብርሃኑ ነጋ ጉራጌ ስለሆኑ ነው " ብለህ ያቀረብከው አመክንዮ በፍጹም አይመስለኝም የሚል ሃሳብ አቀርባለሁኝ።    አንተም እንደምታውቀው "ከኢትዮጵያ ሱሴ ነው" ንቅናቄ በፊት በዓለም ዓቀፍ አሉ የሚባሉ አብዛኞቹ ሙሁራን፤ ውጭም አገር፤ አገር ውስጥም ያለው ኢትዮጵያዊ ተስፋውን ያሳካልኛል ብሎ የሚጠብቀው በፕሮፌሰር ዶር ብርሃኑ ነጋ ስኬት ልክ ነበር። ሚሊዮኖች ከውስጣቸው ያከብሯቸው፤ ከህሊናቸው ይፈቅዷቸው እንደ ነበረ አንተው እራስህ ያዬኽው የሃቅ እንክብል ነበር። አብሶ በአውሮፓ ህብረት የነበራቸው ዕውቅና እና ተቀባይነት ልዩ ነበር።    ሙግታችን ኢትዮጵያን ለመረከብ ጎደለ የምንለውን ንቅናቄያቸው እንዲያስተካክል ነበር። እርግጥ አገር ቤት ከገቡ በኋላ ብዙ ደጋፊያቸውን ለከቅላይ ሚር አብይ አህመድ እንዳስረከቡ ይረዳኛል። የሳቸው ማህበራዊ መሠረት ምንጩ ዜግነት ነበር። አብዛኛው ተስፋ የጣለባቸውም አማራ ነበር።    ደጋፊያቸው፤ አክባሪያቸው አማራ ነበር። ነገር ግን ከአማራ #መደራጀት ጋር በሚነሱ ሃሳቦች ዙሪያ ተስፋ እና ተስፈኛው እንደተፋጠጡ አስተውያለሁኝ። አማራው የራሱን ድርጅት ሲፈጥር በእሳቸው ድርጅት፤ የሳቸው ራዕይ ችግር እንደሚገጥመው ያው...