ስለተከደነ።

እንኳን ደህና መጡልኝ።

ስለከደነ።
„የመከረኝን እግዚአብሄር እባርከዋለሁ።“
መዝሙር ፲፬ ቁጥር ፯
ከሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
 13.03.2019
 ከእመ ዝምታ - ከሲዊዘርላንድ

እንዴት ናችሁ ውዶቼ? ደህና ናችሁ ወይ ዛሬ ከፍቶታል። የደነዘዘው ቀን ነው። እኔም አውሮፕላን አደጋ ሲከሰት ድርጭት ነው የምሆነው። ይጨንቀኛል። ለደረሰው አደጋ ብቻ ሳይሆን የአውሮፕላን አደጋ ሲደርስ እጅግ የሚያሳስበኝ ያን ተከትለው ተጨማሪ ተከታታይ አደጋዎች ደግሞ ስለሚከሰቱ ነው።

ይህ ስለምን እንደሆን እኔ እንደማስበው በሌሎች አገር አብራሪዎች ላይ  አደጋው ተጨማሪ ስትረስ ስለሚፈጥር ይምስለኛል። ስሊዚህ አንድ አደጋ ሲደርስ ተከታይ ሌላ አደጋ ደግሞ ይኖራል የሚል ተጨማሪ ስጋት ያድርብኛል። ያው እኔ የግሎባል የበረራ ቤተኛ ከሆንኩኝ ዓመታት ተቆጠሩ።

ብረሳው፤ ብተወው ደስ ይለኝ ነበር ግን ከነፍሴ ጋር ባላሰብኩበት ሁኔታ ተጠባቀ። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ አዬር መንገድ በድንገተኛው አደጋ ሳይደናቀፍ ተግባሩን በተለመደው መንገድ በትጋት መቀጠሉ በውነቱ የአመራሩን ብቃት ደረጃ ከፍ አድርጎታል። እነ አጅሬ ካለልካቸው ገብተው ደግሞ ለወደፊቱ ካላተራመሱት።


አስደሳች ዜና የተከሰከሰውን አውሮፕላን አስመልክቶ ከአቶ ተወልደ አውን የተሰጠ መግለጫ

የሆነ ሆኖ ዛሬ ምንም ዜና የለም። የኢትዮጵያ መንግሥትም ዜናውን ተግ እንዲል ያስደረገ ይመስለኛል። በተጨማሪነት ሌሎችም ተጨማሪ አገሮችም የተወሰነ ጊዜ ማዕቀብ በቦይንግ 737 ማክስ 8 እንዳደረጉ ዓለም አቀፍ ዜናዎች እዬዘገቡ ነው።

አውስትራልያ፤ ኖርወይ፤ ብራዚል ወዘተ … ቀዝቃዘው ጦርነት ደግሞ በዛው ልክ ይጦፋል … የዝና የገብያ ጉዳይ ነውና … ይህ ደግሞ የድሃ አገሮችን ሊጎዳ ይችላል፤ ወይንም በክፉ ዓይን እንዲታዩ ሊያደርግ፤ ወይንም ባለሰቡት መንገድ ሴራ ሊሸረብባቸው ይችላል። ከገብያ የማስወጣት። ሌላም መደራደሪያ የማስገደጃ ቅደመ ሁኔታ ግዳጅ ሊመጣም ይችላል …

·       ዕለቱን በማስተዋል።

ወደ ዕለቱ ጉዳዬ ስገባ ያው እምከታተለውን ጉዳይ አጠናክሪ መቀጠል ስለሚኖርብኝ ስለ ተከደነው ገመና ላትኩር እሻለሁኝ። አሁን የኢትዮጵያ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ያላትን የፓን አፍረካንስትንትም ለመቀማት ነው ትግል እዬተደረገ ያለው። 

ውድድሩ በኢትዮጵያዊነት እና በኦሮሞዊነት መካካል ነው። ብዙ ሰው አዲስ አባባን ብቻ ነው የሚያው ከዚህ ያለፈ የገዘፍም ጉዳይም ነው። በሰብዕዊነት አንጻርም ሲታይ አውሮፓ በናዚ የከፈለውን ያህል ዋጋ የሚያስከፍል ነው። የዶ/ር ለማ መገረሳ የማህበረሰብ ብወዛ ምህንድስና። ለዚህ ደግሞ በባንዳነት የተሰለፈውን ገመና በዝምታ የ ኢትዮጵያ ህዝብ ስለሚያው ስለ አቶ ንጉሱ ጥላሁን የሴራ ልብነት ትንሽ ትዝብቴን ላጋራችሁ ወደድኩኝ።

በቅድሚያ ግን አቶ ንጉሡ ጥላሁን የአብይ ካቢኔ ደጋፊ አድርጋችሁ የምትስሏቸው ትልቅ ግድፈት እዬፈጸማችሁ ነው። በህይወታቸው የሚጠሏቸው ሰው ቢኖሩ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ጠ/ሚር አብይን አህመድን ነው። ኮንፕሌክስ አላባቸው። በ11 ወር የሥልጣን ዘመናቸው አንድ ጊዜ ነው ሙሉ ሥማቸውን ሊጠሩ የተገደዱት።

ለዛውም ጠ/ሚር ቢሮ ስለገቡ ብቻ። ይህ እራሱ ብርቅም ሆኖብኝ ራሱን አስችዬ ጽፌዋለሁኝ። የ አማራ ክልል እራሱ እንዲታወክ ተግተው እዬሠሩ ነው። ልብ ቢኖረው አዴፓ መጀመሪያ መበጣጠስ የሚኖርበት የአቶ ንጉሡ ጥላሁንን የሴራ መረብ ነው። በስተቀር ዶር አንባቸው መኮነን እጅግ የከፋ አደጋ ነው የሚገጥማቸው። ኢትዮጵያን ለደቂቃ በሥሟ አይጠሯትም ‚አገሪቱ‘ ነው የሚሏት። በጣም ነቀርሳ የሆኑ ሰው ናቸው። እዬጠሏት ነው የሚኖሩባት። 

የኦቦ ንጉሡ ጥላሁን ትናጋ ግድነት - በኦቦነት ግንድነት።

አቶ ንጉሱ ጥላሁን ጃዋርውያን ናቸው። ጃዋርውያን ደግሞ ጠ/ሚር አብይ አህመድ ዋንኛ ጠላታቸው ነው። ቅናትም ኢጎም በበዛ ሁኔታ አለባቸው ጃዋርውያን ይህን አውድዮ ታዳምጡት ዘንድ በትህትና እገልጻለሁኝ።

እንዲያውም የአቶ ንጉሡ ጥላሁ ከልክ በላይ መንፋፋት፤ መቀተት ምንጩ ይህ ያልተገባ የጃዋርውያን ሪኮምዴሽን ነው። ውዶቼ ይህን ከልባችሁ እና ከህሊናችሁ ሆናችሁ መርምሩት። አገር ማለት ሁለመናነት ነው። ከአገር በላይ ሊከበርም፤ ዕውቅና ሊሰጠውም የሚጋባ ጉዳይ ሊኖር አይገባም።



                                                                 አገርን አሳልፎ የመስጠት ተልዕኮ!

https://www.zehabesha.com/amharic/archives/88248

„ሕወሓት ለማ መገርሳን ለጠቅላይ ሚኒስተርነት ለምን አልፈለገችውም?

 – ጀዋር መሐመድ ያብራራል | ከሳዲቅ አህመድ ጋር ተወያይቷል“


አቶ ንጉሡ ጥላሁን አማራን የሚፈልጉት ለኦነግ ገባሪነት ነው። 


ከሀምሌ ጀምሮ የመንፈስ ኩዴታ መካሄዱን በስፋት ስዘግብ ባጅቻለሁኝ ከሥርም የተወሰነውን ሊንክ አስቀምጫለሁኝ። ለኩዴታው እና ለማንኛውም የ ኦነጋውያን የምህንድስና ሴራ ድር ልብ ናቸው አቶ ንጉሡ ጥላሁን። ማንም ሰው ስለ እሳቸው አውቃለሁ የሚለው ብጣቂ ነገር የለም።

እሳቸውን በማቅረብ፤ ዕውቅና በመስጠት እረገድ ዶር ለማ መገርሳም ተባባሪ ናቸው። 
የጃዋር አንደበት የተልዕኮው ማህንዲስ።

ለዚህም ነው ለአቶ ጃዋር በሚሊኒዬም አዳራሽ ቅብጥ እና ቅልጥ ሲባል አቶ ንጉሱ ጥላሁን ከባህርዳር ተነስተው በቦታው የተገኙት በኦነግ ተንሳኤ። ኤርትራም ለማደራደር ዶር አንባቸው መኮነን እና ዶር ገዱ አንዳርጋቸው እያሉ የተላኩት እሳቸው ናቸው። ፕ/ኢሳያስ አፈወርቂ አማራ ክልል ሲገኙ ደግሞ ድብዛቸው አልነበረም … በሁሉም ዘርፍ መፈተሽ ያስፈልጋል - ሚዛናዊ ሆኖ። ምክንያቱም ከጠ/ሚር አብይ ጋር ቆመው መታዬት ሞታቸው ስለሆነ፤ ከጃዋርውያን ማህበርም ስለሚያስገልላቸው። 

በሌላ በኩል አቶ ጀዋር መሃመድ በዓለም የሚጠላው ሰው ቢኖር ጠ/ሚር አብይ አህደመድን ነው። አታስታውሱም የቅዱስ ዮሖንስ የዋዜማ ዝግጅት ተጠርቶ እኮ አልተገኘም። በምን ሁኔታ አቶ ጃዋር መሃመድን ከጠ/ሚር አብይ ጋር ማገናኘት አይቻልም። ምን እና ምናቸው ይገናኛል? ኢትዮጵያ እኮ ለአነጋዊው ጃዋርውያን የጠላት አገር ናት። በተገኙበት ሁሉ መሰበር ነው ቅስሟን። ማንከት ነው አቅሟን። 

ያው እኔ እንደምለው ማእቀቡ አለ፤ ድርጅታቸው ከድቷቸዋል ስለዚህ አሁን በቀረው እንጥፍጣፊ ባትሪ ነው እዬተንቃሳቀሱ ያሉት ጠ/ሚሩ አብይ አህመድ። እሳቸውን ሰቅዘው እንዲይዙላቸው እኮ ነው ፕ/ ለማ መገርሳ አቶ ንጉሡ ጥላሁን የጠ/ሚር ቢሮ የፕሬስ ጽ/ሃላፊ አደርገው የመደቡት። 

ስለማያምኗቸውም ነው ከሀምሌው ዝምታ ጀምሮ ባለው የውጭ ግንኙነት ዘርፍ ከኦዴፓ ውጭ ሌላ ሰው ተጨምሮ የማያውቀው። ይህንንም ማንም ሰው አስተውሎት አያውቅም። አጀንዳውም አይደለም። በተባበሩት መንግሥታት ተናጋሪ ሆነው ተመርጠው እኮ እንዲቀሩ ተደርጓል ጠ/ሚር አብይ አህመድ። 

ቢሞቱላቸው እኮ ነው የሚወዱት። መኖራቸው ነው እንዲህ አግሬሲብ እያደረጋቸውም አለው። ይህን ስል የአቶ አዲሱ አረጋን የሰሞናቱን ንግግር ስቼ አይደለም። ያም ለስልት ይሆናል ስማቸውን ያስገቡት ብዬ ነው እማስበው ... ለድርብ ተልዕኮ።  

ሰከን ብሎ ጉዳዮችን መመርምር ይገባል። አቶ አዲሱ አረጋም ጠ/ሚር አብይ አህመድን አይፈልጉም። ከኦዴፓ ውስጥ ቅን ምልከታ ያላቸው አቶ ካሳሁን ጎፌ ብቻ ናቸው ለዶር አብይ አህመድ - እንደ እኔ ክትትል።

ጠ/ሚር አብይ አህመድ ከፕ/ለማ መገርሳ ጋር ያላቸውም ግንኙነት ቢሆን ሳያስጠጡ ትእዛዝ እዬተቀበሉ መሥራት ነው። ዲዛይነሩ ዶር ለማ መገርሳ ናቸው። የሚተነፍሱት ጠ/ሚሩ በፕ/ለማ መገርሳ ልብ ነው። ይህ ደግሞ ግድ የሆነበት ምክንያት በሀምሌው ዝምታ ምክንያት ነው። 

ጠ/ሚር አብይ አህመድ የራሳቸው የሆነ አቅም፤ ክህሎት፤ ጥበብ ስለሌላቸው አይደለም፤ በቂ አቅም በሁሉም መስክ አላቸው። ይህም ነው  ሊያስገድሏቸው ያሰቡት፤ ሊገድሏቸውም አሰቡ ሞትን አሸንፈው ህይወታቸው ቀጠለ።

እሳቸውን በጠራራ ጸሐይ አውርዶ ፕ/ለማ መገርሳን ማድረግ ደግሞ አሁን በዓለም ያለው ተቀባይነት ምን መልክ ሊኖረው እንደሚችል ሊገምቱት አለመቻላቸው ነው እንጂ ደፋሮች ስለሆኑ ይህንም ማድረግ ሳያስቡ ቀርተው አይደለም። አብዛኛው ቀውስ እኮ እነሱውሰራሽ ነው። ይህም ሆኖ ጠላፊው ቡድን ወይንም እገታ የጣለው አንጃ አይረካም።

ለዚህ ነው ፕ/ ለማ መገርሳን ጠላፊው ቡድን የውጭ ጉዳይ ሚ/ር አድርጎ ለማምጣት የሚሻው። አብይን የጠለፉት ወይንም ያስጠለፉት የራሳቸው ልብ ሊሆን ይችላል።
የሆነ ሆኖ አቶ  አባ ዱላ ገመዳ፤ አቶ ጃዋር መሃመድ፤ አቶ አዲሱ ለገሰ፤ አቶ ንጉሡ ጥላሁን አቶ ለማ መገርሳ፤ አቶ ታከለ ኡማ አንድ ላይ ናቸው። የእነሱን መንፈስ ደግሞ ሳይወዱም በግድ ሳያጋልጡም የራሳቸውን ገመና ድፍን አድርገው ጠ/ሚር እንዲያስፈጽሙ ይፈለጋል። በስተቀር የምትሆነው ትሆናለች። 

ኢትዮጵውያን የሚሰጡትን ማናቸውንም ያልተገደበ አቅሞች፤ መጋቢ ክልሎች የሚሰጡትን ማናቸውንም ድጋፍ ለዶር አብይ አህመድ ሲባል መሆኑንም ጠንቅቀው ያውቁታል ኦነጋውያን። ይህን ለኦሮሞ አገርነት እንዲውል ይሻል የለማ መንፈስ በ አብይ ደጋፊ በ አብይ አድናቂ ያለው የመንፈስ ሃብትን በ አግባቡ ሥራ ላይ በማዋል ህልማቸውን ማሳከት ይሻሉ። ሳይንሱ ይኸው ነው።

አሁን ባልታሰበ ባልጠበቁት ሁኔታ ዕድሜ እና ክብር ለጀግናው ዶር አብርሃም አለሙ ተዝረከረከላቸው። የሚገርመው ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ ሲፎግር የነበረ የኦሮሞ ልጅ አክቲቢስት፤ ጋዜጠኛ፤ ጸሐፊ ሰምቶ ጸጥ ነበር ያለው። ቋንቋውን የሚችሉት ራሱ ድፍን አድርገው ነበር የያዙት። የኢትዮጵያ አምላክ ግን ዘረገፈው። አሁን ሰከን ብሎ አቅም ማዋጣት ለማን አገርነት ብሎ በማስተዋል መመርምር ይገባል። 

ጠ/ሚር አብይ አህመድም ራሳቸውን በንጽህና ግልጽ አድርገው ደፍረው እውነቱን ለኢትዮጵያ ህዝብ መንገር ይኖርባቸዋል። ከ እንግዲህ ወዲህ ብዙም የሳቸውን መንፈስ አጽድቆ የሚቀጥል አቅም የለም። ለስልት ቢያደርጉት እራሱ የሚያዋጣ አይደለም። አገር አደጋ ላይ ናት ያለችው። 

ይህን እኔ በጥዋቱ ጽፌዋለሁኝ። አድማጭ አልነበረም። የፕ/አለማርያም ‚አክ ወሬም‘ ብዙውን አቅም ባልሆነ አቅጣጫ መርቶ  የኦነጋውያን አቅም ጎልብቶ እንዲወጣ አድርጓል። እኔ በጀመርኩበት ጊዜ የሚያግዘኝ ባገኝ ቢያንስ ሚዛኑን የሚያስጠብቅ የሎቢ ተግባር ውጭ ይኖረን ነበር። ጠ/ሚር አብይ አህመድም ከገቡበት ረግረግ ሳይስምጡ ማዳን ይቻል ነበር።

እኔ ለአቶ ኦባንግ ሜቶ ነሃሴ 20 /2018 ደውዬ ነግሬው ነበር። ይህም አለ ብሎ የተደራጀ የሎቢ ተግባር እንዲከወን … ግን አልሆነም በሳምንቱ እሱ ኢትዮጵያ ገባ … የጠ/ሚር አብይ አህመድን አቅም ችሎታ ታጋሽነት ልናጣው አይገባም ነበር። የቀደሙ ተግባራቸውን እና ተቆርቋሪነታቸው አይደለም እኛን አፍሪካም ልታጣው የሚገባ አልነበረም። ስጦታ ነበሩ። ባልሆነ ሁኔታ እና ባልሆነ ጊዜ እዛ ተገኙ እንጂ።

·       ስቅሉ።  

የሆነ ሆኖ በዛ ሰሞን የኬኒያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ኢትዮጵያን ይጎበኙ ነበር።

ጃዋርውያኑ አቶ ንጉሱ ጥላሁን አንገታቸውን ብቅ አድርገዋል።

እሳቸው መጥተው በነበረ ጊዜ ጃዋርውያኑ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ተገኝተው ነበር አብረው፤ ያው ተቸግረው አብረው ከጠ/ሚር አብይ ጎን ተነሰተዋል እንጂ ከ4 ጊዜ በላይ ጠ/ሚር አብይ አህመድ አማራ ክልል ሲገኙ ከ አጠገባቸው ድርሽ አይሉም ነበር።

ሌላው የዛሬ ልባም ጉዳዬ አሁን እሳቸውን በወከለው ለዚህ ደረጃም አንጠራርቶ እስከ መፈንቀለ ኩዴታ አንቱታ ያደረሰው ክልል አማራ የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ሲገኙ ግን ጃዋርውያኑ አቶ ንጉሱ ጥላሁን አልተገኙም፤ ለሳቸው የጣር ያህል ነው።



እሱ ብቻ አይደለም ይህን ያህል መከራ ተጋድሎ ያደረጉት ጓዳቸው ሥልጣናቸውን ፕ/ ገዱ አንዳርጋቸው ለዶር አንባቸው መኮነን ሲያስተላላፉ በሽኝታው ፕሮግራምም አልተገኙም የኦነግ የውስጥ አርበኛው አቶ ንጉሱ ጥላሁን።



ይህም ብቻ አይደለም በጓዳቸው በቆሞስ ተስፋዬ ጌታቸው ህልፈት ጠ/ሚር አብይ አህመድ ለቅሶ ቤት ሲገኙ አሳቸው አብረው አልነበሩም። ጃዋርውያኑ አቶ ንጉሡ ጥላሁንን ለኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ሌላው የተጠመደ ፈንጅ በመሆናቸው በጥንቃቄ በዓይነ ቁራኛ ማዬት ብልህነት ነው።
            ጠ/ሚር አብይ አህመድ በጀግናው በቆሞስ ተስፋዬ ጌታቸው ቤት።

ከሳቸው ጋር ያለውን መረብም እንዲሁ አሁን ደግሞ ለህዝብ ቆጠራ ጉዳይ እጬጌው እሳቸው ሆነው ወጥተዋል፤ ለምርጫውም እሳቸው ናቸው የሚሆኑት … ኦነጋውያን ከሳቸው ሌላ የሚያምነው ሰው በአማራ ክልል የለውም።

 ንጉሱጥላሁናውያን ግን አይጠፉም አብሶ ከአማራ የብዝሃን መገናኛ ድርጅት ውስጥ … ሴራው ያልገባው ልሙጥ። አማራን ለማዘልዘል ይሆናል ከሳቸው ጋር በምንም ዓይነት ጉዳይ መጣመር። እራሱ ሰለሚፈናቀሉት አማራዎች ጉዳያቸው አይደለም። ይህ የ100ሺህ መፈናቀል የማን ጥንስስ ነው ተብሎ በቂ ምርመራ አልተደረገበትም፤ ቀን ጉዱን ያወጣዋል። 

… አማራ አቅም ሲያጣ ኦነጋውያን ጉልበታቸውን የሚፈታትን ይጠፋል … ለዚህ ደግሞ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በባልደራስነት አሉበት … ሰላም ከታወከ እራስ ችሎ መቆም ያቅታል። እንኳንስ ለሌላው ሊኮን። አሁን ብዙዎቹ ብአዴኖች የአዲስ አባባ የኗሪዎቿ ናት ይበሉ እንጂ ኦዴፓ ዘንዶውን አስቀምጧል።

በሌላ በኩል ሌሎች ክልሎችንም በጥበብ ለመያዝ ሌላ መላሾም ይዘጋጃል … ምህንድስናው ለብለብ አይደለም። ስንቱ ሊሂቃን ነው እጅ ሰጥቶ በተገዛለት ፕላስተር አፉን ለጉሞ ደሞዝተኛ የሆነው? ትናንት በእነ አቶ ልደቱ ይሳቅ የነበረው እኮ ዛሬ ዓመት ድገም እያለ ነው … በመንፈስ ጠ/ሚር አብይ አህመድ ብቻ ሳይሆኑ ተፎካካሪ ነኝ የሚለውም ትንፍሽ አይልም እስረኛ ነው የ ኦነጋውያን። ሥጋ እያሳዩ ነው ከአፎታቸው የከተቷቸው።

የሆነ ሆኖ ወደ ቀደመው ነገረ ንጉሱ ስመጣ ምን እዬተከወነ ስለመሆኑ ሌላ ፍንጭ ስለሚሰጥ ጉዳዬ ትሉት ዘንድ ነው ይህን ጹሑፍ የጻፍኩት። ስለተከደነ የሳቸው ገመና ለሰው አጀንዳ ሊሆን አልቻለም። 

እንቅስቃሴያቸውን የኢትዮጵያ ህዝብ በጽኑ ሊከታተለው ይገባል። ለዚህም ደግሞ አዲስ መንፈስ ተነስቷል የአብይ አጀንዳ ፈጻሚ እንደሆኑ አቅጣጫ ለማሳት … አሳቸው ጃዋርውያን ናቸው ፈጽሞ አብያውያን አይሆኑም እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ።

የሳቸው በጠ/ሚር ቢሮ የጽ/ቤት አባል መሆን ማለት አንድ ብርጌድ የጣሊያን ጦር እዛ ተቀመጠ ማለት ነው። እንዲህ ተዛንፎ በዝልቦሽ የሚታይ አይደለም። እሳቸው እዬተጉበት ያለው ማናቸውም ጉዳይ ለውጡን ቀልብሶ ሙሉ ለሙሉ ለጃዋርውያን የማሰጠት ተልዕኮ ነው ይዘው መሽገው ያሉት።

ስለዚህ ህሊና ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ ከቅርንጫፉ ወይንም ከጭፍጫፊው ላይ ሳይሆን ቤተ መንግሥት ሰለል ብለው በገቡት በአቶ ንጉሡ ጥላሁን የክህደት መንፈስ ላይ ሙሉ አትኩሮት እና ክትትል እንዲያደርግ አሳስባለሁኝ - በትህትና። ሊንክ ናቸው እሳቸው ለሁሉም። 

የአባ ገዳ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ሚዲያ AMMA „ፊንፊኔማለትን አህዱ አለ።


የአማራ ቴሌቪዥን እኮ አዲስ አባባን "ፊንፊኔ" ብሎ እስከመጥራት ደርሷለኝ። ሎቱ ስብሃት። መቼም ከዚህ በላይ ውርዴት፤ ከዚህ በላይም ሞት የለም። ይህን የሚያስደርጉት ደግሞ እሳቸው ናቸው። "ልብ ያለው ሸብ።" የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላቱንም ወዳጁንም ለይቶ ማወቅ ይኖርበታል። 

ውዶቼ ፎቶወች ብዙ ነገር ይገልጻሉ እና በ ስተውሎት ውስጡን ዘልቃችሁ ትመረምሩት ዘንድ በትህትና አሳስባችሁአለሁኝ።

እኔ ለውጡ መንፈሱ መፈንቅል ተካሄደበት ብዬ እማስበው ሀምሌ 18 ለሀምሌ 19 ዋዜማ ነው። ጠ/ሚር አብይ አህመድ ጉዞ ላይ ወደ ስሜን አሜሪካ እያሉ። ስጋቴን ስገልጽባቸው የቆዬሁባቸው ጹሑፎች ከብዙ በጥቂቱ እነሆ …

https://sergute.blogspot.com/2018/08/blog-post_18.html

ነፃነት ለአብይ እና ለቤተሰቡ!

18.08.2018

https://sergute.blogspot.com/2018/08/blog-post_65.html

ኡኡ የአድማጭ ያለህ! ሰሚ ቢገኝ! ኦገስት 2018፣ 16 ሐሙስ።

https://sergute.blogspot.com/2018/08/blog-post_76.html

ግልበጣ በዬፈርጁ። ድንግዝግዝ በብርዝ ዲቃላዊ መንፈስ።

16.08.2018 

https://sergute.blogspot.com/2018/08/80.html

ግን እባክህን አትገንግን? 80 ችግር እንደገና ግን?

07.08.2018

https://sergute.blogspot.com/2018/08/blog-post_62.html

የእቅፋት እንቅፋት፤

15.08.2018

https://sergute.blogspot.com/2018/08/blog-post_20.html

20.08.2018

የአዲሲቱ አትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በዶር አብይ ዙሪያ መግለጫ አወጣ!

ንጉሡ ድምጽ አልባ ተውኔት በቤተ - መንግሥትም አና አለብን።


ኢትዮጵያዊነት ከመፈጠሩ በፊት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር!
የኔዎቹ ኑሩልኝ።

መሸብያ ጊዜ። 

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።