ልጥፎች

#ጸጸትን ስለማስተናገድ።

  #ጸጸትን ስለማስተናገድ።    "የእግዚአብሄር ቃል ሁሉ ትፈትናለች፤ እርሱ ለሚታመኑት ጋሻ ነው።" (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፴ ቁጥር ፭)   #ምዕራፍ ፲፱።   የሰው ልጅ በሚያምንበት መስመር መሳተፍ መብት ነው። የሰው ልጅ #በማያምንበት መስመርም ቢሆን ጊዜው // ዘመኑ ካስገደደው መኖርን ለመምራት በሚያደርገው ተጋድሎ ውስጥ ስለመሆኑ አስተውሎ ሊመረምረው ይገባል።   130 ሚሊዮን ህዝብ ከአገሩ ውጭ የት ይሰደድ? ልሰደድ ቢልስ ይችላል ወይ? ይህንን ጽንሰ ሃሳብ በዘመነ ህወሃትም እጽፈው ነበር። የሚቻል ነገር ከገጠመ በህሊና ዳኝነት መወሰን ጥሩ ነው። #በማይቻል ሁኔታ ግን የአንዷን ቀን የለት ጉርስ መሸፈን ጋዳ ሆኖ፤ ተመችቶት በተቀመጠ ድሎተኛ ጫና በራስ ላይ ሌላ ፈተና ማከል አያስፈልግም። ህይወት ጥምልምል ነው። ያ በቂ ነው - ፈተናው።   ስለሆነም ወጣቶች ዕድል፤ ዘመን፤ ሁኔታ የሚፈቅድላችሁን ማድረግ ይገባችኋል። በዘመነ ህወሃት የውጭ የትምህርት ዕድል ያገኜ ወጣት አልሄድም፤ ሥርዓቱን ስለማልወደው አላለም። በዕድሉ ተጠቅሞ ለቤተሰቡም ተስፋ መሆን የቻለው ዕድሉን #ባለማፍሰሱ ነው።   በ6ኛው ይሁን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ መሳተፍ፤ እጩ ሆኖ ለመቅረብ መፍቀድ፤ በድምጽ ሂደቱ ለመሳተፍ በአገኛችሁት ዕድል ሁሉ መሳተፋችሁ ወጣቶች ሆይ! #አይጸጽታችሁ ። በኢትዮጵያ ውስጥ እየኖራችሁ መኖራችሁም እራሱ ፖለቲካ ነውና በሁነታዋ ሁሉ በንቃት መሳተፍ የተገባ ነው። ዕድሉ ከተገኜ።   በሌላ በኩልም በአገራዊ ምክክሩም መሳተፍ መልካም ነገር ነው። በተሳትፎው ውስጥ ትልቁ ቁምነገር በዕድሉ ከክፋ ሃሳብ ጋር አለመገናኘት ግን ይገባል። መሳተፍ ጸጸት #አይደለም ።   ታላቅ ተመክሮ፤ ጥሩ ሰወች ጋ...

አዲስ አበባ #ቅዱስ መንፈስ ናት። ብልህነት ዊዝደም ነው። ብልጥነት ግን ለእኔ እንቅጩን ስናገር #ማጭበርበር ነው።

ምስል
  ብልህነት ዊዝደም ነው። ብልጥነት ግን ለእኔ እንቅጩን ስናገር #ማጭበርበር ነው።   የምርጫ ተርሙስ ከ6ኛው አገራዊ ምርጫ ይጀምራልን???? ሁለት የምርጫ ተርም ወደ ሦስት ማህበረ እንደ ልቡ ካላስደረጉት። የምርጫ ተርሙስ ከሁለት ወደ ሶስት ይሸጋገራልን? ከ7ኛው ምርጫስ ይጀምራልን? በዞግ ፖለቲካ ፕሬዚዳንታዊነት??? በቋንቋ "ፌድራሊዝም" እንደ አሜሪካ ዲሞክራሲ?   "ንጉሥ በፍርድ አገሩን ያጸናል፤ መማለጃ የሚወድ ግን ያፈርሰዋል።" መጽሐፈ ምሳሌ (ተግሳጽ ) (ምዕራፍ ፳፰ ቁጥር ፬)   #በፓርላማ ምርጫ ፕሬዚዳንታዊ???? እንዴት ሊሆን ይችላል?   በቃ ኢትዮጵያ የተፈጠረችው የአንድን ዞግ ፍላጎት፤ ምኞት መሻት ብቻ ልታስፈጽም ነውን? ሌላው ጥያቄዬ ደግሞ መንግሥታዊ አደረጃጀትን ፓርቲያዊ ዲስፕሊን ውስጥ ተዘፈቀን?    ግን ክብረቶቼ እንዴት ናችሁልኝ?    እኔ ሁሉንም ነገር መጀመሪያ ላይ በቅንነት ስለማይ ይህ የፕሬዚዳንታዊ መሻት #በስምንተኛው አገራዊ ምርጫ በእያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ አቶ ሀ፤ አቶ ለ፤ አቶ መ ሴት አይታሰብም ይወዳደሩ እና ያን ጊዜ ፕሬዚዳንታዊ መሆን ይቻላል የሚል ዕሳቤ ነበረኝ።   እንዲህ በአቋራጭ እንደ አየር ላይ ትምህርት ዶክተሬትነት በፍጹም አላሰብኩም። አንድ እንፍራንዝ ከምትባል ትንሽዬ ከተማ የምርጫ ጣቢያ፤ ወይንም አርሲ ከሚገኝ ዲክሲስ ከሚባል የምርጫ ጣቢያ የተመረጠ አቶ ሀ አቶ ለ አቶ መ የአገር ፕሬዚዳንት ልክ እንደ አሜሪካኖች ዲሞክራት፤ ሪፓብሊካን ወይንም ኢንዲፔንደት ልሆን ብሎ ማሰብ ብዙ የገዘፋ የመንግሥት አደረጃጀት መርሆችን የሚሰባብር፤ የሚያቆሳስል፤ የሚገርፍ መከራ ይሆናል።    ብዙ የገዢው ፓርቲ የብልፄው ዝንባሌው የመ...

በፓርላማ ምርጫ ፕሬዚዳንታዊ???? መንግሥታዊ አደረጃጀትን ፓርቲያዊ ዲስፕሊን ውስጥ ተዘፈቀን?

  በፓርላማ ምርጫ ፕሬዚዳንታዊ????    እንዴት ሊሆን ይችላል?    መንግሥታዊ አደረጃጀትን ፓርቲያዊ ዲስፕሊን ውስጥ ተዘፈቀን?   በስምንተኛው አገራዊ ምርጫ በያንዳንዱ የምርጫ ጣቢያ አቶ ሀ፤ አቶ ለ፤ አቶ መ ሴት አይታሰብም ይወዳደሩ እና ያን ጊዜ ፕሬዚዳንታዊ መሆን ይቻላል። እንጂ አንድ እንፍራንዝ ከምትባል ትንሽዬ ከተማ የምርጫ ጣቢያ፤ ወይንም ዲክሲስ ከሚባል የምርጫ ጣቢያ የተመረጠ አቶ ሀ አቶ ለ አቶ መ የአገር ፕሬዚዳንት ልክ እንደ ዲሞክራት፤ ሪፓብሊካን ወይንም ኢንዲፔንደት ልሆን ብሎ ማሰብ ብዙ የገዘፋ የመንግሥት አደረጃጀት መርሆችን የሚሰባብር፤ የሚያቆሳስል፤ የሚገርፍ መከራ ይሆናል።   ብዙ ዝንባሌው የመጫን መንፈስ ከኖረው መንፈስ፤ አየር ይወጠራል። የተወጠረ አየር መተንፈሻ ቧንቧ ሲያጣ ይፈነዳል። አሁን ባለው ግሎባል ይሁን አህጉራዊ፤ አህጉራዊ ይሁን ብሄራዊ ትብትብ ችግር አብዝቶ ማስተዋልን፤ አብዝቶ አርቆ አሳቢነትን፤ አብዝቶ ብልህነትን እንጂ ብልጥነትን አይጠይቅም። ብልጥነት ለእኔ አጭበርባሪነት ነው። ማጭበርበር ከገብያ ሂደት ጋርም መራራ ነው እንኳንስ በመንግሥት አደረጃጀት።

"፭ #መቶወቹ።" #ትንሽዬ ዕይታ።

  "፭ #መቶወቹ ።"   "እግዚአብሄርም አለ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር።"    (ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፳፮)   የሰው ጉዳይ፤ የተፈጥሮ ጉዳይ የራስ #እንደራሴነት ጉዳይ ነው። ለእኔ። ሥጦታ የአጋይሥት ዓለሙ ሥላሴም ነውና።   "እግዚአብሄርም አለ፤ #ሰውን በመልካችን እና #ምሳሌያችን እንፍጠር።"   #ትንሽዬ ዕይታ።    እንዴት ነን? አንድ አገር ነው ያለን። አንድ ማዕድ ነው ያለን። አንድ እልፍኝ ነው ያለን። ስለሆነም #አግለን ይሁን #አቅርበን ልናየው የምንችል አመክንዮ ቢኖርም የእናት ጉዳይ ግን #አናት ነው። ልናደምጠው፤ ልንከታተለው፤ ሰሙን አልሰሙን ዕይታችን ማጋራቱ የቤታዊነት ልዕልና ጋር ያገናኛል እና ሁኔታውን መከታተሉ ይጠቅማል። የዜግነት #እኩሌታ ወይንም #እርቦ ይሁን #ሲሶ ስለለው።    #የኮሚሽኑ ዕለታዊ ማብራሪያ።   "አዳሪ አጀንዳወች ሊኖሩ ይችላሉ። ለቀጣዩ ትውልድ ም ሊሻገሩ የሚችሉ።" የሁለንም ኢትዮጵያዊ ዜጋ #ሰብሳቢ የሚያደርገው #በክብነት ውስጥ #ማዕዳዊ የማድረግ አቅም ያለው፤ እኛን ኢትዮጵውያንን ብቻ ሳይሆን #አፍሪካውያንንም እንዲሁም ሉላዊ የዲፕሎማት ፬ኛ ግሎባል መዲናይቱን፤ ባለቤት ወይንም #ተጠማኝ ሊያደርግ የሚችል የምክር ሃሳብ ሊሆን ይችል ይሆን #አዳሪ ይሁን ተገፍቶ በቀጠሮ ለቀጣይ #የትውልድ #ቀጣይ የቤት ሥራ ሊሆን የሚችለው?    ፊት ለፊት ተገናኝቶ መነጋገሩ መልካም ነው እንጂ፤ በጠቅላይ ሚኒስተሩ በኦሮምያ ያደረጉት ንግግር ተስፋው የገዘፈ ፈተና ሥራ ላይ እያለ ሳይቀር እንዳለበት ይገልፃል። በትርጉም ነው የሰማሁት። የነበረን ለማስቀጠል ድካሙ ይሁን ወ...

"የሰይጣን ጆሮ ይደፈን።" አሜን። "#እንጨራረሳለን።" አንባሳደር ባጫ ደበሌ በኬኒያ የፈላስፊት ኢትዮጵያ ባለሙሉ አንባሳደር (ጄኒራል)

  "የሰይጣን ጆሮ ይደፈን።" አሜን። " #እንጨራረሳለን ።" አንባሳደር ባጫ ደበሌ በኬኒያ የፈላስፊት ኢትዮጵያ ባለሙሉ አንባሳደር (ጄኒራል)   "ስለዚህም ነገር ፆምን፥ ወደ እግዚአብሔርም" ለመንን፤ እርሱም ተለመነን።" (መጽሐፈ ዕዝራ ምዕራፍ ፰ ቁጥር ፳፫)   ምዕራፍ ፲፱።   • https://www.youtube.com/watch?v=f4ydQf__UDA “ጦርነት ከተጀመረ መንግሥታት ይለወጣሉ፤ ድንበሮች ይቀየራሉ”| BBC News አማርኛ (በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ)   «ቢቢሲ በኢትዮጵያ እና በቀጣናዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርጓል። የኢትዮጵያ አሁናዊ ሁኔታ፣ ከህወሓት ጋር ያለው ውዝግብ፣ የባሕር በር ጥያቄ እና የቀጠናዊ የጦርነት ስጋቶች በቃለ መጠይቁ ተዳሰዋል።»   #ዕፍታ ።   ደንግጬ ነው ያዳመጥኩት። በሚሊተሪ፤ በባንክ፤ በመንበረ - መንግሥት፤ በአፍሪካ ቀንድ ፖለቲካ እጅግ ቁጥብ ነኝ። በሰባዕዊ መብት ጉዳይ፤ ወይንም በፖለቲካ ፓርቲ አደረጃጀት እና አመራር ነው ገፋ ያለ ጊዜየን የምመግበው።    " #እንጨራረሳለን ።" አንባሳደር ባጫ ደበሌ (ጄኒራል።)   ማነው ጨራሹ?   ማንስ ይሆን ተጨራሹ? እጅግ አስጨናቂ አገላለጽ ነው። "የሚጨራረሰው" የሰው ልጅ ነው። ኢትዮጵያዊው ሰው። ሰሞኑን ብልፄው የግሪን ሌጋሲውን ሂደት የመራበት ሞቶ "ተስፋን #እንትከል ነው።" ለሞቶ #ቅሸራ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ A+ ናቸው።    ሳይንስ እና ቴክኖሎጂም ሚኒስተር በነበሩበት ጊዜም "ከእርምጃ ወደ ሩጫ" የሚል ሞቶ እና ኮንፍረንስ ነበራቸው። ለትውልድ የሚሆን ቋሚ የሥራ ባህል ...