#ዘመነ #ሰማዕትነት በየለቱ #በየባዕቱ። #በዚህ መሰል ሂደት መሬትም --- ታዝናለች። አየሩ --- ያዝናል። ተፈጥሮ --- ያዝናል። ዘመንም --- ያለቅሳል። ፈጣሪም ይከፋል።

 

"አቤቱ የቤትህ ቅናት በላኝ።"
 
የምህረት፤ የይቅርታ፤ #የይቅርባይነት ልቦና ፈጣሪ ለሁላችንም
ይስጠን። አሜን። 
 
#ምዕራፍ ፲፱።
 
ሰማዕታት በዘመኑ በርካቶች ናቸው። ጥቂቶችን ብቻ ነው ያቀርብኩኝ።
ሁሎችም ምንም #ከፖለቲካ ጋር ግንኙነት ዬሌላቸው #ባተሌወች ነበሩ።
 
ሁሎችም እናት አላቸው። ስለ ኢትዮጵያ እናቶች ይጨንቀኛል።
ሴቷ ካረሳሁት ዕጸገነት የምትባል፥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ
ሠራተኛ #ሙሽራም የነበረች ነበረች። 
 
ታዳጊ ወጣቱ ወላጆቹን እየሠራ የሚረዳ ነበር። በዚህ ዕድሜው
የቤተሰብ #ኃላፊነት የወሰደ ትጉህ ነበር።
 
እስር ቤት ውስጥም #ሰማዕትነት የተቀበሉ የባንክ ሠራተኛም አሉበት።
በአማራ ፖለቲካ ይመስለኛል ታሥረው የነበሩት።
 
ፈውስ፤ መፍትሄ፤ መዳን፤ ርህርህና፤ ዕውቀት ሁሉም ነገር እንዳልነበረ
የሆነበት የሃኪሞች ጉዳይ የኢትዮጵያ የተስፋዋ #ውጋት የሆነ ገጠመኝ ነበር፤
የሁሎችም ሰማዕትነት በአማራ ክልል የተከወነ ነው። 
 
"ህወሃት በፖለቲካ የበላይነት" በሚመራበት የአማራ ክልል ይህን መሰል #ጥቃት
የሚጠበቅ ነው።
 
በሱር ኮንስትራክሽን በማዕከላዊ ጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ 80ሺህ ተፈናቃይ እስከ ስሜን ፓርክ ቃጠሎ
ድረስ የተከወኑት አሰቃቂ፤ ሰላም ነሽ ጉዳዮች ባለቤቱን በእርግጠኝነት መናገር አይቻልም #የተቀየጠ ስለሆነ። 
 
ለነገሩ አቤቱ ህወሃት ናፍቀህናል #ና እባክህ #ናልን መባሉን እያዳመጥን ነው። 
 
የሆነ ሆኖ በሁሉም ሂደት የሰው ልጅ እንዲህ በየለቱ ተስፋውን ማጣቱ እጅግ …… እጅግ
ያሳዝናል። ዕድሜው እንዲህ መቀጨቱ። ትናንት በጉራጌ ዞን ነዋሪ የሆኑ አማራወችም
እንዲሁ #ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። 
 
ብሄራዊ - አገራዊ - ኢትዮጵያዊ ምምክር እየተደረገ ባለበት በአሁኑ ወቅት፤ 
ይህን መሰል #የነፃ #እርምጃ ድንገተኛ ነገር አሳሳቢ ነው። 
 
ፈፃሚው "በየመንግሥት ወታደሮች" ናቸው የሚል አንብቤያለሁኝ።
ዜናውን ያዘገየሁት ከBBC ማረጋገጫ እየጠበቅሁ ነበር። የሆነ ሆኖ #ሰባዕዊነት
እና #ነገ ምን እና ምን ናቸው ኢትዮጵያ ላይ????
 
መንግሥት አምነው ለተቀመጡ ኢትዮጵያዊ ዜጎች የደህንነት #ዋስትናቸውን ከማን
ይጠብቁ? 
 
ይህን መሰል ሂደት በጥንቃቄ ሊታይ ይገባዋል። ምክንያቱም ለራሱ
ለኢትዮጵያ መንግሥት ስለማይጠቅም። 
 
በህወሃት የማብቂያ ዘመን የጸጥታ ሠራተኞች ሰብአዊነትን ይማሩ ዘንድ 
ውጭ አገር የሆነ ዕድል ተመቻችቶ ነበር። 
 
መጨረሻም የህወሃት ዘመን #ተጠናቀቀ። ከዚህ ትምህርት መውሰድ ይገባል።
አሁን ቅርብ ጊዜ ምርጫ ያካሄደ መንግሥት ብዙ ችግሮችን ይሁን
ፈተናወችን አስታግሶ መያዝ ይገባዋል። ይህን ሲያደርግ ተጠቃሚው
እሱ እራሱ መንግሥት ነው። 
 
ነገን አብዝቶ #በርህርህና ማሰብ ይገባል። የኢትዮጵያ #እናቶችን ማሰብ ይገባል።
የተዋህዶ ልጆች ጥብቅ ሱባኤ ላይ ናቸው። ይህንንም እንደ አገር ማሰብ ይገባል። ፆም
ላይ ጭካኔ???? 
 
ሌላው መጪው አዲስ ዓመት ነው። አንዱ ነጭ ለብሶ ሌላው #ጥቁር ተስፋን ይፈትናል።
መተዛዘን፤ መተሳሰብ እንጂ #መጨካከን ፈጽሞ የማይጠቅም ጎዳና ነው።
 
በሰው #እጅ ሞት ሊቆም ይገባል - በኢትዮጵያ። በኢትዮጵያ የፖለቲካ #እስረኛም ሊኖር
አይገባም። ተከራከሩ - በነፃነት፤ ተሟገቱ - ተደማምጣችሁ። ጠቃሚው ነገር ስለ
#ነገ ይህ ብቻ ነው። 
 
#በዚህ መሰል ሂደት
መሬትም --- ታዝናለች።
አየሩ --- ያዝናል።
ተፈጥሮ --- ያዝናል።
ዘመንም --- ያለቅሳል።
ፈጣሪም ይከፋል። 
 
አንድ ሰውን ደግሞ ማግኜት አይቻልም። ሞት መራራ ብቻ ሳይሆን ለቤተሰብ
እንደ ገል መንፈስን ወደ ስብርባሪ የሚቀይር ጨካኝ ክስተት ነው።
 
ለወላጆቻቸው መጽናናትን እመኛለሁኝ። 
 
የሃዘን ዳርቻ ፈጣሪ ያድርግልን። አሜን።
 
ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን።
ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።
ኑሩልኝ። አሜን።
ሥርጉተ©ሥላሴ።
Sergute©Selassie.
12/08 /026.
በቃችሁ ይበለን አምላካችን አላሃችን። አሜን

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።