"ከበላይ አካል #የመጣ " በትዕዛዝ ፍላጎትን ማሳካት ከሆነ ስለምን #ኮሚሽን ተቋቋመ???

 የአዲስ አበባን ጉዳይ ቅርቃር ውስጥ ያስገባው "ከበላይ የመጣ" ሃሳብ እና የምክክር ኮሚሽኑ ምላሽ - BBC News አማርኛ

"ከበላይ አካል #የመጣ " በትዕዛዝ ፍላጎትን ማሳካት ከሆነ ስለምን #ኮሚሽን ተቋቋመ???
 
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
 
#እኮ……… እኮ።
 
#የምክክር ኮሚሽኑ "የበላይ አካል" ማን ነው?
አቶ ሽመልስ አብዲሳ?
አቶ አዲሱ አረጋ?
ከንቲባ አዳነች አበቤ ወይንስ ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ?
እንዲህ በሥርዓት ውስጥ ያላለፈን አጀንዳ በትዕዛዝ ከመፈጸም ይልቅ
እነ ብልፄው #በዓዋጅ የምትፈልጉትን መፈጸም ይቻል ነበር እኮ? ይህ ሁሉ ወጪ ከሚወጣ?
#ስድስት ዓመት? አይጣልን ያቀላል ሰው።
 
የፕሬዚዳንቱ የሥልጣን ዘመን 6 ዓመት የሚለው ሃሳብ #ሞናትነስ ነው። አይጣልባት ለጦቢት። አሜን።
5 ዓመትም በጣም #አሰልቺ ነው።
 
ከዚህ ለዚህ ፓርላማው #ሺህ አመት ይንገሡልን ብሎ ቢያጸድቅም ይቻላል። የኤርትራ የመንግሥት አያያዝ እንዲህ
#ተናፋቂ ከሆነ። በብልፄው ፓርላማ ለሙሉ መዋዕለ ዕድሜ ብሎ ማስወሰን። በቃ #አቋራጩ መንገድ ይህ ነው።
#ከምክክሩ እንወጣለን" ስለሚሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ጉዳይ።
 
" አይጥ ወልዳ ወልዳ ከጅራቱ ስትደርስ" ዓይነት ነው። መገኜታችሁ #የተገባ ጉዳይ ነበር። እስከ ፍፃሜ መዝለቅም
#የተገባ ነው። ልቅ ሐረግ ነው የሚሆነው። መቋጧ የለሽ።
 
በስማ በለው ምን ተባለ ከማለት ባለው ዕድል ተጠቃሚ መሆን አትራፊ ነው። ምንጊዜም። ስለ እናት ጉዳይ አጀንዳ
የሁሉም #ልጆቿ ሊሆን ይገባል። እራስን ባይታዋር ማድረግ አይገባም። መሳተፍ ይገባል።
 
የቀሩት ገብተው ቢሆን ከዚህ የተሻለ ጠንካራ #ጣዕም ያለው የሙግት ሃሳብ ይደመጥ ነበር። በሌላ በኩል
ይህ ዕድል #የቱሪዝንም ተግባር ከውኗል።
 
በመገኜታችሁ አስባችሁ ወይንም አቅዳችሁ የማታገኟቸውን #ውድ እና #ክቡር ወገኖቻችን ጋር መተያዬት ችላችኋልል።
ፖለቲካ ከሰውነት በታች እንጂ በላይ አይደለምና። መተያዬቱ "ነገር በዓይን ይገባል" ይላሉ ባለቅኔወች ጎንደሮች። 
 
ስለሆነም በተለይ #እናት ፓርቲ ምክክሩን ጥሎ እንዳይወጣ በአጽህኖት፤ በትህትናም ላሳስበው እሻለሁኝ። ኩርፊያ፤
ቁጣ፤ ቅያሜ በእናት ጉዳይ የተገባ አይደለም። "ዙሮ ዙሮ ከቤት።"
 
መገኜት፤ ማየት፤ ማድመጥ፤ ሃሳብን በቅጡ አደራጅቶ ማቅረብ፤ ጥቂቱ ለብዙኃን ውሳኔ ተገዥነትን መፈጸም
ይገባል። የዴሞክራሲ አስተምኽሮ ይህ ነው። ተጫኝ ሃሳብ ምክክሩ ካጠቃው ሳይለንት ዲስክርምኔሽን ይጋበዛል።
ይህ "ከበላይ አካል መጣ" #ልግጫ እና የገበጣ ጨዋታ ግን ከሥርዓት ያፈነገጠ #አናርኪያዊ ጉዳይ ነው።
 
#አናርኪዝም ከሚሳኤል በላይ አቅም አለው ለማደፍረስም ይሁን ለመበተን።
 
ቸር አስበን፤ ቸር እንሁን። አሜን።
ቅን አስበን፤ ቀና እንሁን። አሜን።
ኑሩልኝ። አሜን።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ። አሜን።
ሥርጉተሥላሴ።
Sergute©Selassie.
13/08/026.
ኢትዮጵያዊነት ከመፈጠሩ በፊት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር ነው።
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።
See less

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።