ልጥፎች

መረጃ በወቅቱ ካልቀረበ ይፋድሳል፤ ዕሴቱንም ይቀንሳል፤ በሌላ በኩል አንድ ሥርዓተ #መንግሥት ሥርዓትን መፍቀድ ግዴታው ነው።

ምስል
  መረጃ በወቅቱ ካልቀረበ ይፋድሳል፤ ዕሴቱንም ይቀንሳል፤ በሌላ በኩል አንድ ሥርዓተ #መንግሥት ሥርዓትን መፍቀድ ግዴታው ነው።   "እግዚአብሄር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም።"       #ምዕራፍ ፲፰።   #እፍታ ።   የዶክተር ገዱ ምስክርነት እና የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ የመስካሪ ፈላጊ ሂደት ምን ያመሳጥርልናል?   #ተመክሮዬ ።   እንዴት ናችሁ ማህበረ ቅንነት? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ።    አንድ ጭብጥ በጣም ሲገርመኝ ሰነበተ። የእኔ የህይወት ተመክሮ የፖለቲካ ፓርቲ ቋሚ እና መደበኛ ሠራተኛ ስለነበርኩኝ ድርጅቴ ኢሠፓ ለተልዕኮ ሲያሰማራኝ ከቡድን መሪ፤ የቡድን ጸሐፊ ጋር ነበር። በተጨማሪም እራሳቸውን ችለው የሚጓዙ ቲሞች ከኖሩም ከፖለቲካ ድርጅቱ በቀጥታ አመራር የሚያገኙ ወደ ተግባር ከመሰማራታቸው በፊት ወጥ የሆነ የተልዕኮ አቅጣጫ ይሰጣቸዋል።   ከተልዕኮ መልስም ሪፖርት ማቅረብ ግዴታቸው ነው። የአቅም ማኔጅመንት የሚታቀደው፤ የሚፈጸመው ከጉዞው #ግብረ መልስ ይሆናል። እኔ የቡድን መሪ ሆንኩኝ፤ ወይንም ሌላ የቡድን መሪ ኖረኝ የማይጓደልበት የዲስፕሊን መርኽ ድርጅቴ ኢሠፓ ነበረው። ለዚህ ነው እኔ የፖለቲካ ፓርቲዬ ኢሠፓ መራራ ስንብት ካደረገ በኋላ በድንግልናዬ የቀጠልኩት። እንኳንስ ፓርቲ የሆነ ተቋም አባልም፤ አካልም መሆን እማልፈቄደው የተፈጠርኩበት ድርጅቴ የፖለቲካ ዲስፕሊኑ፤ ተመክሮው፤ እኛን የቀረጸበት መንገዱ አንቱ ነበር። ከጠቀመ ላጋራችሁ ፈቀድኩኝ።    1) እኛ ለተልዕኮ ስንላክ የተልዕኳችን አጠቃላይ መንፈስ #ይነገረናል ። ሁላችንም በተልዕኳችን ላይ #እኩል ግንዛቤ እንዲኖረን የወል ማብራሪ...

"#ይሁነኝ #ብለን" (ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ) የምርጫ ማዕከላዊ #መርህ #ከቀናው ሙግቱ ተጀምሯል።

ምስል
  " #ይሁነኝ #ብለን " (ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ) የምርጫ ማዕከላዊ #መርህ #ከቀናው ሙግቱ ተጀምሯል።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ። አሜን።"   ሰላማዊ የፖለቲካ ተፎካካሪ ፓርቲወች በ2018 ምርጫ ለመሳተፍ ሙሉ ፈቃደኝነት ማሳየታቸው የፖለቲካ #ብልህነት ነው። ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲወች በስማ በለው ሳይሆን የዕድሉ ባለቤት ሆነው ዕድላቸውን #ሳያፈሱ በዕድሉ ሊጠቀሙ ይገባል። ይህ ሂደት ፖለቲካዊ #ብልህነትም ነው። ሰላማዊ ትግል ለመረጠ አንድ የፖለቲካ ድርጅት ዓላማ እና ግቡን #ለማስተዋወቅ ፤ #ከቀናው #ለመፈጸም እና ለማስፈጸም ብቸኛ ጎዳናው #ምርጫ ብቻ ነው።   በምርጫ መሳተፍ ብዙ በጣም ብዙ ትርፎች ሲኖሩ እንዲህ በመንግሥት ሚዲያ #ዕድሉን ሲያገኙ የማኒፌስቷቸውን ጭብጥ #ቀለል ባለ አገላለጽ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማቅረብ ይችላሉ። ደጋፊወቻቸው ያነቃቃሉ። የፖለቲካ ባህል ይዳብራል።    ለተፎካካሪ የፖለቲካ ሊቃናት ይሁን ለገዢው ብልጽግና ሊቃናት የልምድ፤ የተመክሮ፤ የንግግር ጥበብ ባህል የሚማሩበት፤ የሚያሳድጉበት ነው። በመሸነፍ ውስጥ ማሸነፍ፤ በማሸነፍ ውስጥ መሸነፍ እንዳለ ዕውቅና ሊሰጡት ይገባል።   ገዢው ፓርቲ ብልጽግና ማዋከብ፤ ጫና ማድረግ፤ ማሰር መፍታት፤ ማስፈራራት አይኖርበትም። በተለይ የታችኛው አካላቱ ይህን መንገድ አካላቱ ስለሚከተሉ " #ይሁነኝ " ብለን መርህ ይከበር ዘንድ ክትትል ሊደረግበት ይገባል።    ብልጽግና በማየው ልክ #ምንም የሚያሰጋው ነገር ያለ አይመስለኝም። 50+ የማግኜት ዕድሉ ሰፊ ነው። ስለዚህም በሆደ ሰፊነት ምርጫው ካለምንም ጫና ለውጤት ይበቃ ዘንድ #ትዕግሥቱን #ሥራ ላይ ሊውል ይገባል ባይ ነኝ።   ከምርጫ ጋራ በተ...

#ማካካሻ። ፲ አለቃ መሳፍንት

ምስል
  #ማካካሻ ።   "አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።   #ምዕራፍ ፲፰።     ፲ አለቃ መሳፍንት ይመስለኛል ሥሙ። የጄኒራል ሳህረ መኮነን ጠባቂ የነበረ ወጣት ነው። እኔ #ታቅዶ የተመደበ ይመስለኛል። ከእሱ ይልቅ ለመታመን ሌሎች ተመሳሳይ ማዕረግ ያላቸው ነበሩ የወንዝ ልጆች ነበሩና። ጄኒራሉን ለመቅደም #ገዳዩ #ጎንደሬ መሆኑ የትወናውን ሁነት ያብራራል።   በሌላ በኩል አገዳደሉን ማን ይምራው ማን? በፍጹም እርግጠኛ የሚያደርግ ነገር በሰውኛ #ስሌታዊ አመክንዮውን ስለማይደፈር። ወላጅ እናቱ ክፍትፍት ባለ #ጉሮኖ ይኖራሉ። አሁን በምን ሁኔታ እንደሚገኙ አላውቅም።   የፍርድ ውሳኔው ተሻሽሎለታል። እግሩ እና ዓይኑ ግን #በድብደባ ብዛት እንደተጎዳ ሰምቻለሁኝ። ደብዳቢወቹ ማን ሊሆኑ እንደሚችሉ የፋክት መረጃ ማቅረብ ባይቻልም፤ በቀልን የጸነሱ፤ መበቀልን በእጥፍ ለመተግረብ የጭካኔ ረሃብተኞች እንደሚሆኑ ግን መገመት ይቻላል። ለኢትዮጵያ የፓርቲ ፖለቲካ ልኳ አይደለም፤ ለእኛም አንመጣጠንም የምለውም ለዚህም ነው።   ህወሃትን ያህል የሴራ #ጉድጓድ ተሸክመህ፤ ሌላውን ቤርሙዳ ትርያንግሉን የማህበረ ኦነግን #ትብትብ አቅፈህ ይህ ብላቴና ግርማቸው የሚያስፈራውን መኮነን ደፍሮ ገደለ ለእኔ ብዙም ቅርብ ያልሆነ ሎጅክ ነው።   መሪነት በግርግር ጊዜ ያላጠናቸውን፤ ግን የገደፋቸውን ስርክራኪ ሁነቶችን እንዲህ ቅንጡ ሆቴሎችን ለመመረቅ ሰፊ ጊዜ ሲሰጥ ደግሞ #ተግ ብሎ እንደነዚህ ዓይነቶችን እጅ እና እግር አልቦሽ የሆነ የበቀል መገበሪያ፤ #የቁርሾ ማካካሻ በሆኑ ዕውነቶች ላይ ጥርት ያለ የግንዛቤ ለውጥ አምጥቶ እራስን ማረመን - ይጠይቃል።   ለመሆኑ ይህ ወጣት አሁን በምን ሁኔታ ላ...