#ነገን #ስለማትረፍ። ስለሰው ልጅ ታላቅነት ዕውቀት የሰው ልጆች በጣም #ያንሰናል።
1) የፍቅር ተፈጥሮ #ካሪክለም ተነድፎለት እያንዳንዱን ልጅ በትምህርት ቤት ማስተማር ይገባል ብዬ ሙግት ከጀመርኩ 15 ዓመት ተቆጠረ።
2) በሌላ በኩል ህግ የጥቂት ሙያተኞች ብቻ ሳይሆን #የማህበረሰቡ ይሆን ዘንድም ከአጸደ ህፃናት ጀምሮ እያንዳንዱ ልጅ በአገሩ #ህገ መንግሥት እና #በታህሳስ 10/1948 ዓለም ዓቀፋ ድንጋጌ ታንጾ ሊያድግ ይገባል።
እኔን መሰል ሙሉ ዕድሜ ላይ ለምንገኝ ደግሞ በፓናል ዲስከሽን፤ በሰሚናር፤ በጉባኤ በየቀበሌው መሠረታዊ የፍቅር ተፈጥሮ እና የህግ ጉዳይ #ልንማር ይገባል። ስለ ሰው ልጅ ታላቅነት እውቀት በጣም ያንሰናል።
አንድ ሰው ግዴታውን ካላወቀ ወንጀል ሊሠራ ይችላል። ህግ ከታወቀ ግን ዓይን ይከፈታል። መብትእና ግዴታን አጥርቶ ማወቅ ይቻላል። ፍጽምነት ባይኖር በአንፃርነት።
#መማር፤ #ማወቅ ጥቁር እና ነጩን መለየት ይቻላል። ይህን መሰል አሰቃቂ ወንጀል ምንጩ አንድም #የህግጋትን ድንጋጌወች አለማወቅ፤ በሌላም #ጥላቻን #የሚነቅል ተቋም ዓለማችን ስሌላት ነው፤ እንዲህ ትውልድ #መርዶ ስንቁ እንዲሆን የተደረገው።
በውነቱ አውስትራልያ ይህን መሰል አሰቃቂ ሃዘን ብዙ የማይገጥመው አገር ነበር። እጅግ አሳዛኝ ጥቁር ዕለት ነው ለአውስትራልያውያን እና ለመላ የዓለም ህዝብም።
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
ሥርጉትሻ 2025/12/15
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ